የዓለም ዜና DW.COM | Deutsche Welle
-
- News
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
-
የዓለም ዜና፦ሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሚያዚያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የላስታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው መልሴና የወረዳው ጤና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ እንዲሁም የራያ አላማጣ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ ደርበው ሰሞኑን በታጣቂዎች ተግደለዋል ሲሉ ነዋሪዎች ለዶቼቬለ ገልጸዋል።
የጋዛው ጦርነት ጦርነቱ ዛሬ ቢቆም እንኳን የወደሙትን ቤቶች መልሶ ለመገንባት ቢያንስ 16 ዓመታት ሊወስድ እንደሚችል የተመድ አስታወቀ።
የአውሮጳ ኅብረት ለሊባኖስ አንድ ቢሊዮን ዩሮ ወይም 1.07 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የፋይናናስ እርዳታ ለመስጠት ቃል ገባ። -
DW Amharic የሚያዝያ 23 ቀን 2016 የዓለም ዜና
የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያውያን የቪዛ አሰጣጥ ሒደት እንዲጠብቅ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዲያጤን ኢትዮጵያ ጠየቀች። የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንቶች 6 ሚሊዮን ዶላር ለማጭበርበር የተደረገ ሙከራ ማክሸፉን አስታወቀ። ከ7 ሚሊዮን በላይ ደቡብ ሱዳናውያን የምግብ ዋስትና እጦት ሊገጥማቸው እንደሚችል ተመድ አስጠነቀቀ። እስራኤል በጋዛ ወደምትገኘው ራፋ ያቀደችውን ወታደራዊ ዘመቻ አሜሪካ አሁንም እንደምትቃወም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ገለጹ። ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት የማረከቻቸውን የምራባውያን የጦር መሣሪያዎች፣ ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች እና ወታደራዊ ሠነዶች በሞስኮ ለዕይታ አቀረበች።
-
-
DW Amharic የዓለም ዜና፤ የሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ሰኞ
--የአውሮጳ ህብረት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች የሚሰጠውን ቪዛ ለመገደብ መወሰኑን ዛሬ አስታወቀ። --በኬንያ ስምጥ ሸለቆ ከተማ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ ግድብ ተንዶ በትንሹ 42 ሰዎች ሞቱ። -ቡርኪናፋሶ ወታደራዊ ጁንታ የዶቼ ቬሌን ራድዮ ጨምሮ የተለያዩ ዓለምአቀፍ የዜና ማሰራጫዎችንና ጋዜጦችን ማገዱ አስታወቀ። -የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የእስራኤል እና የሃማስ ጦርነት ሲያበቃ፤ ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር በጋዛ ጉዳይ ላይ ለመምከር በሳዑዲ ዋና ከተማ ሪያድ መግባታቸዉ ተዘገበ።
ዝርዝሩን ያድምጡ! -
DW Amharic የሚያዝያ 20 ቀን 2016 የዓለም ዜና
በኬንያ ከመጋቢት ጀምሮ እየጣለ የሚገኘው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 76 አሻቀበ። ሱዳን በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች “ትንኮሳ” ላይ የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት በአስቸኳይ እንዲወያይ ጥያቄ አቀረበች። የፖርቹጋል መንግሥት አፍሪካውያን በባርነት ሲሸጡም ሆነ በቅኝ ግዛት ወቅት ለተፈጸሙ ወንጀሎች ካሳ ለመክፈል ምንም አይነት ሒደት እንደማይጀምር አስታወቀ። ወግ አጥባቂው የእስራኤል የፋይናንስ ሚኒስትር ቤዛሌል ስሞትሪች በራፋ የታቀደው ወረራ ከተሰረዘ የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁን መንግሥት እንደሚያፈርሱ ዛቱ። ሁለት ዩክሬናውያን በላይኛው ባቫሪያ በስለት ተወግተው መገደላቸውን የጀርመን ፖሊስ አስታወቀ።
-