Voice of Truth and Life Donatist
-
- Religion & Spirituality
Being a light in this world.
-
እግዚአብሔር በተናገረው ውስጥ ራስን ማግኘት
የአንድ አማኝ መንፈሳዊ ሀብቱ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ራስን በእግዚአብሔር ቃል ተስፋ በመለኮት ሀሳብ ውስጥ ማግኘቱ ነው
-
የጥሞና ጊዜ,,,ካለፈው የቀጠለ
የጥሞና ጊዜ በእግዚአብሔር ላይ የማረፍ ህይወት ነው የጥሞና ጊዜ የለመዱ ሰዎች ፊቱን ይናፍቃሉ በእግሩ ስር መሆን ይወዳሉ ደስታና እረፍት በመንገዳቸው ነው አይናወጡም ሁሉን በሚችል አምላክ ጥላ ስር ናቸው
-
ጥያቄ እና መልስ ክፍል 95
የዛሬ ጥያቄዎች
1. ምሳሌ 30፡11-12 በወላጆቻቸው የተጎዱ ልጆች የእግዚአብሔር በረከት እንዲያገኛቸው እንዴት ነው እንደዚህ ዐይነት ልጆችን ማገልገል የምንችለው?
2. በግልፅ የሚደረግ ፀሎትና በስውር የሚደረግ ፀሎት ብታብራራልን? እንዴት ነው እንደዚህ ዐይነቶች ፀሎት መፀለይ የምንችለው?
3. ምሳሌ 31፡1-5 ልጅን በማሳደግ ውስጥ ልጆች በሚያልፉበት መንገድ የወላጆች ድርሻ በተመለከተ ምን ትመክረናለህ?
4. ከውጪ ያየነውንወደ ቤተ ክርስትያን ስላመጣነው ምን ትመክረናለህ?
5. ምሳሌ 31፡13 በማጉረምረም እና በማረም ላይ ልጅን በማሳደግ ላይ ያለው ልዩነት ምንድን ነው? -
ጥያቄ እና መልስ ክፍል 96
የዛሬ ጥያቄዎች
1. ጌታ የሰጠን ፍቅር እሱን ብቻ እንድንወድ ሳይሆን የእርሱ የሆኑትን ጭምር እንጂ የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
2. የእርሱ የሆኑትን መውደድ የምንቸገረው ለምንድን ነው?
3. 1ኛ ቆሮንቶስ 1፡4 ያደገ ሰው በሞተ ፍቅር ላይ ህይወትን ይዘራር የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
4. የእግዚአብሔር እረፍት በእኛ የሚሆነው እሱ በአለን ውስጥ ስንገኝ ነው የሚለውን ሀሳብ አብራራልን።
5. ራሳችንን እግዚአብሔር በተናገረን ካላየን መስኮት እንደሌለው ቤት ነው የምንሆነው የሚለው ሀሳብ ይብራራልን።
6. ዮሐንስ 5፡5 መንፈሳዊ ነገር ስንሆን አስመስለን የምንለው ነገር አለ እና ይህ ይብራራልን።
7. መኋልየ መኋልይ ዘሰለሞን 4፡12-16 የመከራ እና የድርቀት ንፋስ ካለመጣ ነገራችን አይከፈትም ወይ? -
የሰው ልጅ የጠፋውን ሊፈልግና ሊያድን መጥቷል
የውስጥ ጥማት ካለ ለኔ አይሆንም የምንለው ምንም ነገር የለም፣ እግዚአብሔር ዘኪዮስን በጊዜው እንደጎበኘው፣ እኛ ክርስቶስን ለማግኘት ፍላጎትና ጥማት ይኑረን እንጂ ጌታ ማንንም አያሳፍርም፣ እርሱን ለማየት ብዙ ነገሮች በዙሪያችን ቢጋርዱን እንኳን የልባችንን መሻት የሚያውቅ አምላክ እግዚአብሔር በጊዜው በዙሪያችን ከጋረዱን ነገሮች አልፎ ወደእኛ ይመጣል
-
ስለ መለኮት ጥበቃ
እግዚአብሔር ያለውን የምንሆነው በመለኮት ጥበቃ ውስጥ እንዳለን አይናችን ሲበራ ብቻ ነው፣ ያለዚያ እንታወካለን፣ ለፈቃዱ ወይም ለተጠራንበትም መኖር አንችልም፣ አይናችን ሲበራ ግን እራሳችንን ከሐጢያት የምንጠብቅበት ወይም ክፉውን የምንጸየፍበትና እግዚአብሔርን በመፍራት የምንኖርበትን ማስተዋልና ጥብብን የተቀበልነው ከመለኮት መሆኑን እንረዳለን፣ በእርሱም አርፈን እንኖራለን