• በኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ከወሰዱ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች መካከል 8.4 በመቶው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባ ውጤት ማግኘታቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። • የመሐመድ ሐምዳን ደጋሎ የሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል በሀገሪቱ ደቡባዊ ክፍል የሚገኙ ቁልፍ የብሔራዊው ጦር ይዞታዎች እና የህዝብ መገልገያ የመሰረተ ልማቶችን በድሮን እንዳጠቃ አንድ ከፍተኛ የጦር መኮንን ተናገሩ። • እስራኤል በጋዛ ማዕከላዊ ክፍል የምትወስደውን ወታደራዊ እርምጃ ስታጠናክር የከተማዋ ነዋሪዎች ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ለቀው መውጣት ጀመሩ ።