SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ

"ለመላ ኢትዮጵያውያን መልካም አዲስ ዓመት! አብረን እናሳልፍ፤ አንድ ጎረቤት አንድ ጓደኛ ይዛችሁ ኑ፤ በባሕላችሁ ተደሰቱ!" የአዲስ ዓመት ቅበላ አስተባባሪ

አቶ ካሪም ደጋል፣ የኢትዮጵያ አዲስ ዓመት ክብረ በዓል አስተባባሪ ኮሚቴ ዳይሬክተር፤ አቶ ኃይለሰማዕት መርሃጥበብ፣ በቪክቶሪያ የኢትዮጵያውያን ማኅበር ዋና ፀሐፊና የአዲስ ዓመት አስተባባሪ ኮሚቴ አባል፤ ወ/ሮ ማርታ ከበደ፤ የአዲስ ዓመት አስተባባሪ ኮሚቴ አባልና የመድረክ መሪ፤ በሜልበር ፉትስክሬይ ክፍለ ከተማ ቅዳሜ ሴፕቴምበር 6 / ጳጉሜን 1 በሚካሔደው የአዲስ ዓመት ቅበላ ልዩ ዝግጅት ላይ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች እንዲገኙ ይጋብዛሉ።