SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ

የአባቶች ቀን አከባበር በሀገረ አውስትራሊያ

አቶ ጉግሳ አሊጋዝ "ለኢትዮጵያውያን ሁሌም የአባቶች ቀን ነው። እኛ ጥሩ አባቶች ነን። ልጆቼን እጅግ በጣም ነው የምወዳቸው፤ በእዚህ ምድር ላይ በጣም ያስደሰተኝ ነገር ቢኖር ከልጆቼ ጋር ያሳለፍኩት ጊዜ ነው " ሲሉ፤ አቶ ኃይለማርያም ኃይለየሱስ በበኩላቸው "እግዚአብሔር በልጆች ባርኮኛል፤ ልጆቼን በፍቅር ነው ያሳደግኳቸው። የወላጅ ግዴታዬን ተወጥቻለሁ ብዬ አስባለሁ። ልጆቼም ለእኔ ትልቅ ፍቅርና አክብሮት አላቸው፤ የአባቶችን ቀን በጣም ደስ ብሎኝ ነው ያከበርኩት" ይላሉ።