የዓለም ዜና

የመስከረም 8 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

የአፍሪካ ኅብረት በሱዳን የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ እና በሀገሪቱ የሚመራ ውይይት ለማስጀመር ጥረቱን እንደቀጠለ የኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ ተናገሩ። ኮንጎ ውስጥ በድጋሚ የተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ በአጭር ጊዜ ውስጥ የበርካቶች ህይወት መቅጠፉን የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ። ሳዑዲ አረቢያ እና የኑኩልየር የጦር መሳሪያ የታጠቀችው ፓኪስታን አንዱ ሌላውን ካልታሰበ ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል ነው የተባለለት ስምምነት ደረሱ ።