የዓለም ዜና

የመስከረም 9 ቀን 2018 የዓለም ዜና

አርዕሥተ ዜና፣ -ከሁለት ሳምንት በፊት አዲስ አበባ ዉስጥ የታሰሩ ሁለት ኢትዮጵያዉያን ጋዜጠኞች ፍርድ ቤት በዋስ እንዲለቀቁ ቢወስንም አለመለቀቃቸዉን ባልደረቦቻቸዉ አስታወቁ።የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች ጋዜጠኞቹ እንዲለቀቁ እየጠየቁ ነዉ።---የጋዛ ጦርነት ለዛላቂዉ እንዲቆም፣እስራኤል ለጋዛ ሕዝብር ርዳታ እንዳይደርስ የጣለችዉ እገዳ እንዲነሳና ሐማስ ያገታቸዉ እስራኤላዉን እንዲለቀቁ ለፀጥታዉ ጥበቃ ምክር ቤት የቀረበዉን ረቂቅ ዉሳኔ ዩናይትድ ስቴትስ ዉድቅ አደረገችዉ።----ሳዑዲ አረቢያ የሚደርስባትን ጥቃት ለመከላከል የፓኪስታንን የኑክሌር መሳሪያና ዕዉቀት ልትጠቀም እንደምትችል ኢስላምአባድ አስታወቀች።