ሙጃ፥ ሰሜን ወሎ በመንግሥት ጦር እና በፋኖ ታጣቂዎች ውጊዪያ እየተደረገ ነው፤ መቐለ፥ ስምንት የሲቪል ማኅበራት ለሰላም ጥሪያቸው በጎ ምላሽ አለማግኘታቸውን ዐሳወቁ፤ ፓሪስ፥ የፈረንሳይ የቀድሞ ፕሬዚደንት አምስት ዓመት ተፈረደባቸው፤ ሮም፥ ጣሊያን እና ስፔን ለጋዛ ሠርጥ ነዋሪዎች ርዳታ የጫነች መርከብን ለማገዝ የጦር መርከቦችን አሰማሩ፤ ጋዛ፥ በእሥራኤል ጦር ጄቶች ጥቃት ቢያንስ 17 ሰዎች ተገደሉ፤ ዴልሂ፥ ሕንድ ሕይወት ያጠፋ ነውጥ በተቀሰቀሰባት ላዳክህ ውስጥ አስቸኳይ ጊዜ አወጀች