የዓለም ዜና

የመስከረም 14 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የኢትዮጵያ ፀጥታ አስከባሪዎች ከሶስት ሳምንት በፊት ያሰሯቸዉ ሁለት የሸገር ኤፍ ኤም ጋዜጠኞች ዛሬ በዋስ ተለቀቁ።ጋዜጠኞቹ እንዲለቀቁ የተለያዩ መገናኛ ዘዴዎችና የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ተቋማት ሲጠይቁ ነበር።-ለጋዛ ሕዝብ ርዳታ ጭነዉ የነበሩ ጀልባዎችን የእስራኤል ጦር በሰዉ አልባ አዉሮፕላን ደብድቧል መባሉ እንዲጣራ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠየቀ---።የእስራኤል ጦር ዛሬ ጋዛ ዉስጥ 40 ሰዎችን ገድሏል።---የሩሲያና የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) አባል ሐገራት ጠብና ፍጥጫ እየከረረ ነዉ።ትንሺቱ የቀድሞ የሶቭየት ሕብረት ሪፐብሊክ ኢስቶኒያ ከሩሲያ ጋር የሚያዋስናትን ድንበር እያጠረች ነዉ።