የዓለም ዜና

የመስከረም 18 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

• በአማራ ክልል በሰሜን እና ደቡብ ወሎ ዞኖች በመንግስት የጸ,ጥታ ኃይሎች እና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ግጭት መባባሱን ናዋሪዎች ተናገሩ ። • የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት «ባንዳ » ያላቸው ኃይሎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እውን እንዳይሆን ለማደናገር» ይጥራሉ ሲል ከሰሰ። • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ዛሬ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ባደረጉት ግጭት ሰዎች ሳይቆስሉና ሳይሞቱ እንዳልቀረ የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ ፡፡ • አሜሪካ በጋና ላይ የጣለችውን የቪዛ ገደብ ማሻሻሏን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።