የዓለም ዜና

የመስከረም 19 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

• የኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በሱዳን የከፋ የጎርፍ አደጋ እንዳይከሰት ተከላክሏል ሲሉ የውሃ ሃብት ሚንስትሩ ሃብታሙ ኢተፋ ተናገሩ ። • በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ ትናንት እሁድ ለተቃውሞ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር ግጭት ገብተው 3 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች አራት ሰዎች ቆሰሉ ። • የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 18 በመቶ የነበረውን የባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ጣሪያ ወደ 24 ከመቶ ከፍ ማድረጉን አስታወቀ።