የዓለም ዜና

የመስከረም 6 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና

የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት ሀገሪቱ ነጻነቷን ካገኘችበት ጊዜ ጀምሮ በሚሊየኖች የሚቆጠር ዶላር መዝረፋቸውን የተመድ አስታወቀ። የጁባ መንግሥት ክሱን አስተባብሏል። እስራኤል ዛሬ በማለዳ ጋዛ ከተማ ላይ የተገመተውን የምድር ጥቃት ጀመረች። እርምጃዋ ከተመድ ጠንካራ ትችት አስከትሏል። ባለፈው ዓመት ጀርመን ውስጥ በተካሄደ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የፖሊስ መኮንን በስለት ወግቶ የገደለ የአፍጋኒስታን ዜጋ በዛሬው ዕለት የዕድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት። የታሊባን መሪዎች በአንድ የአፍጋኒስታን ክፍለ ሀገር ውስጥ ገመድ አልባ የኢነርኔት አገልግሎት ወይም ዋይፋይ አገዱ። ምክንያቱ ኢስነምግባራዊነትን ለመከላከል የሚል ነው።