SBS Amharic - ኤስ.ቢ.ኤስ አማርኛ

ግማሽ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ግምት ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶች ከአውስትራሊያ ወደ ድሬዳዋ ድል ጮራ ሆስፒታል እያመሩ ነው

በሜልበርን አውስትራሊያ የፉትስክሬይ ሮታሪ ክለብ ዓለም አቀፍ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ጃማ ፋራህ፤ የድሬዳዋን መርጃና መደጎሚያ ማኅበር በአውስትራሊያ ተጠሪዎች፤ አቶ ሳምሶን ከበደና አቶ ዳዊት ከበደ ስለምን ለድሬዳዋ ድል ጮራ ሆስፒታል የሕክምና ቁሳቁሶችን ለመላክ እንደተነሳሱ ይናገራሉ።