Continental Drift

Eden Teshome

''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.

  1. MAR 16

    የባህረ ሰላጤው የኢነርጂ ቀውስ እና የአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ተጋላጭነት

    በመካከለኛው ምስራቅ የሚከሰት ግጭት እንዴት በአፍሪካውያን የዕለት ተዕለት ኑሮ፣ በትራንስፖርት እና በምግብ ዋጋ ላይ ቀጥተኛ ጫና ይፈጥራል? የዓለም የነዳጅ ገበያ መናጋት አፍሪካ የራሷን የኢነርጂ መሠረተ ልማት እንድትገነባ እና በውጭ ገበያ ላይ ያላትን ጥገኝነት እንድትቀንስ የማንቂያ ደወል ሊሆን ይችላል? "በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ የሚታየው ከፍተኛ መዋዠቅ፣ በተለይም እንደ አፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ባሉ ማዕቀፎች ውስጥ ጠንካራ የአህጉር አቀፍ የኢነርጂ ትብብር እንዲኖር እንደ ማነቃቂያ ሊያገለግል ይችላል። እዚህ ላይ አንድ ዋና ነጥብ መጥቀስ እንችላለን፤ ምክንያቱም ከውጭ በሚገቡ ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት መቀነስ አስፈላጊ ነው፤ ረጅም ጊዜ የሚወስዱ ዓለም አቀፍ የዋጋ ድንጋጤዎች በእነዚህ ምርቶች ላይ ጥገኛ የሆኑ ሀገራትን ተጋላጭነት ጎልቶ እንዲወጣ ያደርጋሉ። በመሆኑም በጋራ ቀጠናዊ የነዳጅ ማጣሪያ ተቋማት እና ድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ ትስስር አማካኝነት ቀጠናዊ የኢነርጂ ትብብርን ማጠናከር ይገባል።" ሲሉ በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረ-ኢኮኖሚ ተመራማሪው መሐመድ ኢብራሂም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በዓለም የነዳጅ አቅርቦት እና በአፍሪካ ኢኮኖሚ ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ከአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የማኅበረ-ኢኮኖሚ ተመራማሪው መሐመድ ኢብራሂም ጋር በጥልቀት እንመረምራለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

    1 hr
  2. MAR 6

    መካከለኛው ምስራቅ ፦ የዓለም አቀፍ የሕግና ሥርዓት ዕጣ ፈንታ ነጋሪ

    በመካከለኛው ምስራቅ እየታየ ያለው ቀውስ የአንድ ቀጠና ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፤ የተመሰረተው ዓለም አቀፍ የሕግ ሥርዓት ታላቅ ፈተና ነው። በኢራን ላይ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች እና እየተባባሰ የመጣው ውጥረት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ቻርተርን እና የሉዓላዊነት መርሆዎችን አደጋ ላይ ጥሏቸዋል። "ሩሲያና ቻይና ሁነቶቹን በቅርበት እየተከታተሉ መሆናቸውና ከትዕይንቱ በስተጀርባ የራሳቸውን ሚና እየተጫወቱ መሆናቸው በጣም ግልጽ ነው። ከሚታየው ነገር ባሻገር ጠልቀን ማየት አለብን። በአንድ በኩል በዩናይትድ ስቴትስና በእስራኤል፣ በሌላ በኩል ደግሞ በኢራን መካከል በመካከለኛው ምስራቅ እየተከሰተ ባለው የፖለቲካ ቀውስ ቻይና እና ሩሲያ በዝምታ ተቀምጠዋል ብዬ አላስብም፤ ምክንያቱም ይህ ቀጠና ለዓለም አቀፍ ፖለቲካ በጣም ስሜታዊ ስፍራ ነው።" ሲሉ አብዱ መሐመድ (ዶ/ር) ፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የመካከለኛው ምስራቅ ውጥረትን እና የዓለም አቀፍ ሕግጋት መሸርሸርን በተመለከተ ከሁለት ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ሳይንስ ባለሙያዎች — አብዱ መሐመድ (ዶ/ር) የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ እና ከዳዊት መዝገበ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ጋር በጥልቀት እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  3. MAR 3

    የዓድዋ ድልና የዘመኑ የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት፦ ያልተቋረጠው የሉዓላዊነት ትግል

    የዓድዋ ድል ከጦር ሜዳ ስኬት በላይ፤ አፍሪካውያን የሉዓላዊነት ድርድር የማይደረግበት መሆኑን ለዓለም ያወጁበት የታሪክ ምዕራፍ ነው። ዛሬስ ሉዓላዊነት ሲባል ግዛትን ከመጠበቅ ባለፈ የኢኮኖሚ ፣ ባህል ጥንካሬን እና በሌሎችም ሉዓላዊ ነን ? ወይስ አሁንም በ"ስልጣኔ" ስም በሚቀርቡልን የዲፕሎማሲ ወጥመዶች ውስጥ ተይዘናል? "ጤነኛ አእምሮ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ በዚያ የአውሮፓውያን ዲፕሎማሲ ውስጥ እንዳይዘፈቅ። እንዳትዘፈቁ! ምክንያቱም አባቶቻችን በምኒልክ ዘመን ያለ ጫማ፣ ያለ ሱፍ ልብስ፣ ያለ ከረባት የአውሮፓውያንን፣ የምዕራብ አውሮፓውያንን ተንኮል ማየት ይችሉ ነበር። እኛ ግን በዚህ ሁሉ ዲግሪ፣ በዚህ ሁሉ ሱፍ እና ዘመናዊ መኪና እነዚህ ሰዎች የሰለጠኑ ስለሚመስሉን ተንኮላቸውን ማየት ተስኖናል። አይደለም፣ እነሱ አረመኔዎች ናቸው። እውነቱን እንጋፈጠው፤ ይህ አረመኔነት ነው።" ሲሉ የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ፣ ደራሲ እንዲሁም የቱሪዝም ባለሙያ እና የባህል ጉዳዮች አንቂ ራስ ዐቢይ ጥላሁን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የዓድዋን ድል ትርጉም ከወቅታዊው የአፍሪካ ሉዓላዊነት ትግል ጋር በማገናኘት፤ የፓን አፍሪካኒዝም አቀንቃኝ፣ ደራሲ እንዲሁም የቱሪዝም ባለሙያ እና የባህል ጉዳዮች አንቂ ራስ ዐቢይ ጥላሁን ጋር በጥልቀት እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

    1 hr
  4. MAR 2

    ዓድዋ:- የሉዓላዊነት መሠረትና የፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አቀጣጣይ

    የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም የተመዘገበው የዓድዋ ድል ጣሊያንን በጦር ሜዳ የማሸነፍ ጉዳይ ብቻ አይደለም።አፍሪካውያን በራሳቸው መደራጀት እና ማሸነፍ እንደሚችሉ ለዓለም ያሳዩበት የታሪክ ምዕራፍ ጭምር እንጂ። ዛሬም ግን የሉዓላዊነት ጥያቈ መልኩ ብዙ ሆኖ እያየነው ነው። "አፍሪካ ምንም ዓይነት ይቅርታ ሳትጠይቅ በጠንካራ አቋም ወደ ድርድር ጠረጴዛው መምጣት አለባት። እነዚህን ሐሳቦች ስላስተዋወቅን ብቻ ‘ባህላዊ’ ጉዳዮች ሊባሉ አይገባም፤ ምክንያቱም ይህ ማንነታችን በመሆኑ ወሳኝ ነው።[...]‘ጭራው ውሻውን እንዲያወዛውዝ’ መፍቀድ የለብንም።" ሲሉ ፓን-አፍሪካዊትና የሕግ ባለሙያ ደስታ መጉዎ (ዶ/ር) ለስፑቲክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የዓድዋን ድል ከወቅታዊው የአፍሪካ ሉዓላዊነት ትግል ጋር በማገናኘት ከፓን-አፍሪካዊትና የሕግ ባለሙያ ደስታ መጉዎ (ዶ/ር) ጋር በጥልቀት እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  5. FEB 4

    አዲሱ የአፍሪካ ሉዓላዊነት ንቅናቄ፡ የሳህል ቀጠና፣ ሩሲያ እና የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም ፍጻሜ

    ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በምዕራባውያን ላይ ያነሱት የሉዓላዊነት ጥያቄ የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካ ቀይሮታል። ለዘመናት "ፀረ-ሽብር" በሚል ሽፋን የተካሄደው የሀብት ዘረፋ እና ጣልቃ ገብነት ሲያበቃ፣ ሀገራቱ ፊታቸውን ወደ ሞስኮ አዙረዋል። ለመሆኑ ይህ የሽግግር ወቅት ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት እና ለባለብዙ ዋልታ የዓለም ስርዓት ምን ትርጉም አለው? " የሩሲያና የአፍሪካ ግንኙነት የሚወሰነው በሩሲያና በአፍሪካ መሪዎች ነው። እና ይህ መሰረታዊ ነገር ነው። የሁለቱ ማለትም ሩሲያ እንደ አንድ ሀገር፣ አፍሪካ እንደ ብዙ ሀገር—የሚሰጡት፣ መሪዎቻቸው የሚወስኑት ነገር ወደፊት የሁለቱን ግንኙነት... የሚወስን ይመስለኛል።" — ፕሮፌሰር ዘነበ ክንፉ፣ በሩሲያ የኢትዮጵያውያን ማህበር ፕሬዝዳንት እና በሩሲያ የስቴት ዱማ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አማካሪ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የሳህል ሀገራት ኮንፌዴሬሽን (AES) ምስረታን፣ የሩሲያን የ"ያለ ጣልቃ-ገብነት" የአጋርነት መርህ እና የአፍሪካን አዲሱን የነጻነት ትግል ከፕሮፌሰር ዘነበ ክንፉ ጋር በሰፊው እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  6. JAN 28

    የገንዘብ ህትመት በሀገር ውስጥ፡ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት አዲሱ ምዕራፍ

    ኢትዮጵያ የራሷን ገንዘብ ኖት በሀገር ውስጥ የደረሰችው ውሳኔ፣ ከውጭ ኩባንያዎች ጥገኝነት የመላቀቅ እና የገንዘብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። ይህ ውሳኔ ከዶላር ጥገኝነት ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። በሌላ በኩል Make Africa Borderless Now ''አሁን አፍሪካን ንብር የለሽ እናድርጋት ንቅናቄ'' አህጉሪቱን ትስስር ዕውን ለማድረግ እየሰራ ነው። "የራስን ገንዘብ ማተም ካልተቻለ ፣ በራስ ገንዘብ መበደር ፣ መገበያየት እና መቆጠብ ካልተቻለ ፤ ሉዓላዊነት እንደ ሀገር አደጋ ላይ ይወድቃል።[...] የራስን ገንዘብ ማተም የራስን ሀገር በራስ አቅም ከማስተዳደር ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው።" ሲሉ መርዕድ ፍቅረዮሐንስ፣ የፕራግማ ኢንቨስትመንት አማካሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማተም የመጀመር ዉጥኗን ትርጓሜ ከኢንቨስትመንት ባለሙያው መርዕድ ፍቅረዮሐንስ ጋር እንፈትሻለን።እንዲሁም አፍሪካን ለትስስር ማነቆ የሆነውን የድንበር ሀሳብን ስለሚታገለው ንቅናቄ ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር ባን ዴንግ (ዶ/ር)ጋር እንወያያለን ። በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  7. JAN 22

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ነፃ ንግድ ቀጣና ፡- ኢትዮጵያ የአፍሪካ እድገትና ሉዓላዊነት ማዕከል የመሆን ውጥን

    ኢትዮጵያ በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸውን ምርቶች ለማንቀሳቀስ ስታቅድ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደግሞ የአፍሪካን የአቪዬሽን ታሪክ የሚቀይር ግዙፍ የኤርፖርት ፕሮጀክት ጀምሯል። እነዚህ የአየር እና የየብስ መሰረተ ልማቶች ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና ለአፍሪካ ትስስር ያላቸው ፋይዳ ወሳኝ ነው፣የኢኮኖሚ ዞኖችም ቁልፍ ሚናን ይጫወታሉ። "ኢትዮጵያ በአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ማዕከላዊ ሚና መጫወት አለባት። ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ኢትዮጵያን የአፍሪካ ማኑፋክቸሪንግ እና የሎጂስቲክስ ማዕከል እንድትሆን ይረዱናል።[...] የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በመጠቀም ያለንን አቅም ወደ ተጨባጭ ውጤት መቀየር አለብን።" ሲሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሰሀ ይታገሱ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው ዝግጅታችን፣የኢትዮጵያን የኢንደስትሪ ልማትና ከአህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት ተጠቃሚነት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሰሀ ይታገሱ (ዶ/ር) ጋር እንመለከታለን። አዲሱ የኤርፖርት ፕሮጀክት ለአፍሪካ አቪዬሽን ያለውን ፋይዳም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ያስተላለፉትን መልእክት እንቃኛለን። በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  8. JAN 15

    የዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ እንቅስቃሴ በአፍሪካ፡- 'ኢትዮ ፔይ' ከዶላር ጥገኝነት ነጻ ለመሆንና ለፋይናንስ ሉዓላዊነት

    የ'ኢትዮ-ፔይ' መጀመር ኢትዮጵያ በዶላር ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥናል። በሌላ በኩል፣ ሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ብርሃን ባልታደሉበት አፍሪካ፣ የኢነርጂ አቅርቦትንና ብቃትን ማሳደግ ወሳኝ የቤት ሥራ ሆኗል። "በዶላር ላይ ጥገኝነት አይኖርም... ቴክኖሎጂው ክፍያዎች በቀላሉ እንዲተላለፉ ያስችላል። ነገር ግን ወደ ተግባራዊ ትግበራው ስንመጣ፣ የሕግ ማዕቀፍ ጣልቃ ገብነት ያስፈልገዋል። በህግ በኩል፣ ሁለቱ ሀገራት ክፍያው እንዴት እንደሚፈጸምና የገንዘብ ምንዛሪው እንዴት እንደሚሆን መስማማት አለባቸው።" ሲሉ የኢት-ስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዝግጅታችን፣ 'ኢትዮ-ፔይ' ስለሚፈጥረው ዕድል ከኢት-ስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ጋር እንወያያለን። ቀጥለን የአፍሪካን የኢነርጂ እንቅፋቶችን ከ'ሰስተነብል ኢነርጂ ፎር ኦል' የኢነርጂ ብቃት ባለሙያ ኤልዛቤት ዋንጌሲ ቼጌ እና ከደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ እና ኢነርጂ ምክትል ሚኒስትር ሳማንታ ግራሃም-ማሬ ጋር እንፈትሻለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr

About

''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.