Continental Drift

Eden Teshome

''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.

  1. 3D AGO

    አዲሱ የአፍሪካ ሉዓላዊነት ንቅናቄ፡ የሳህል ቀጠና፣ ሩሲያ እና የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም ፍጻሜ

    ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በምዕራባውያን ላይ ያነሱት የሉዓላዊነት ጥያቄ የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካ ቀይሮታል። ለዘመናት "ፀረ-ሽብር" በሚል ሽፋን የተካሄደው የሀብት ዘረፋ እና ጣልቃ ገብነት ሲያበቃ፣ ሀገራቱ ፊታቸውን ወደ ሞስኮ አዙረዋል። ለመሆኑ ይህ የሽግግር ወቅት ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ነጻነት እና ለባለብዙ ዋልታ የዓለም ስርዓት ምን ትርጉም አለው? " የሩሲያና የአፍሪካ ግንኙነት የሚወሰነው በሩሲያና በአፍሪካ መሪዎች ነው። እና ይህ መሰረታዊ ነገር ነው። የሁለቱ ማለትም ሩሲያ እንደ አንድ ሀገር፣ አፍሪካ እንደ ብዙ ሀገር—የሚሰጡት፣ መሪዎቻቸው የሚወስኑት ነገር ወደፊት የሁለቱን ግንኙነት... የሚወስን ይመስለኛል።" — ፕሮፌሰር ዘነበ ክንፉ፣ በሩሲያ የኢትዮጵያውያን ማህበር ፕሬዝዳንት እና በሩሲያ የስቴት ዱማ የአፍሪካ ጉዳዮች ምክር ቤት ከፍተኛ አማካሪ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የሳህል ሀገራት ኮንፌዴሬሽን (AES) ምስረታን፣ የሩሲያን የ"ያለ ጣልቃ-ገብነት" የአጋርነት መርህ እና የአፍሪካን አዲሱን የነጻነት ትግል ከፕሮፌሰር ዘነበ ክንፉ ጋር በሰፊው እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  2. JAN 28

    የገንዘብ ህትመት በሀገር ውስጥ፡ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት አዲሱ ምዕራፍ

    ኢትዮጵያ የራሷን ገንዘብ ኖት በሀገር ውስጥ የደረሰችው ውሳኔ፣ ከውጭ ኩባንያዎች ጥገኝነት የመላቀቅ እና የገንዘብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። ይህ ውሳኔ ከዶላር ጥገኝነት ለመውጣት ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። በሌላ በኩል Make Africa Borderless Now ''አሁን አፍሪካን ንብር የለሽ እናድርጋት ንቅናቄ'' አህጉሪቱን ትስስር ዕውን ለማድረግ እየሰራ ነው። "የራስን ገንዘብ ማተም ካልተቻለ ፣ በራስ ገንዘብ መበደር ፣ መገበያየት እና መቆጠብ ካልተቻለ ፤ ሉዓላዊነት እንደ ሀገር አደጋ ላይ ይወድቃል።[...] የራስን ገንዘብ ማተም የራስን ሀገር በራስ አቅም ከማስተዳደር ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አለው።" ሲሉ መርዕድ ፍቅረዮሐንስ፣ የፕራግማ ኢንቨስትመንት አማካሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማተም የመጀመር ዉጥኗን ትርጓሜ ከኢንቨስትመንት ባለሙያው መርዕድ ፍቅረዮሐንስ ጋር እንፈትሻለን።እንዲሁም አፍሪካን ለትስስር ማነቆ የሆነውን የድንበር ሀሳብን ስለሚታገለው ንቅናቄ ከጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህር ባን ዴንግ (ዶ/ር)ጋር እንወያያለን ። በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  3. JAN 22

    የኢንዱስትሪ ፓርኮች እና ነፃ ንግድ ቀጣና ፡- ኢትዮጵያ የአፍሪካ እድገትና ሉዓላዊነት ማዕከል የመሆን ውጥን

    ኢትዮጵያ በድሬዳዋ ነጻ የንግድ ቀጣና ከ4 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸውን ምርቶች ለማንቀሳቀስ ስታቅድ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ደግሞ የአፍሪካን የአቪዬሽን ታሪክ የሚቀይር ግዙፍ የኤርፖርት ፕሮጀክት ጀምሯል። እነዚህ የአየር እና የየብስ መሰረተ ልማቶች ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት እና ለአፍሪካ ትስስር ያላቸው ፋይዳ ወሳኝ ነው፣የኢኮኖሚ ዞኖችም ቁልፍ ሚናን ይጫወታሉ። "ኢትዮጵያ በአፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስር ማዕከላዊ ሚና መጫወት አለባት። ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች ኢትዮጵያን የአፍሪካ ማኑፋክቸሪንግ እና የሎጂስቲክስ ማዕከል እንድትሆን ይረዱናል።[...] የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነትን በመጠቀም ያለንን አቅም ወደ ተጨባጭ ውጤት መቀየር አለብን።" ሲሉ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሰሀ ይታገሱ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው ዝግጅታችን፣የኢትዮጵያን የኢንደስትሪ ልማትና ከአህጉራዊ የነጻ ንግድ ቀጣና ስምምነት ተጠቃሚነት ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሰሀ ይታገሱ (ዶ/ር) ጋር እንመለከታለን። አዲሱ የኤርፖርት ፕሮጀክት ለአፍሪካ አቪዬሽን ያለውን ፋይዳም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ያስተላለፉትን መልእክት እንቃኛለን። በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  4. JAN 15

    የዲጂታል ፋይናንስ ዘርፍ እንቅስቃሴ በአፍሪካ፡- 'ኢትዮ ፔይ' ከዶላር ጥገኝነት ነጻ ለመሆንና ለፋይናንስ ሉዓላዊነት

    የ'ኢትዮ-ፔይ' መጀመር ኢትዮጵያ በዶላር ላይ ያላትን ጥገኝነት በመቀነስ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ የምታደርገውን ጉዞ ያፋጥናል። በሌላ በኩል፣ ሚሊዮኖች የኤሌክትሪክ ብርሃን ባልታደሉበት አፍሪካ፣ የኢነርጂ አቅርቦትንና ብቃትን ማሳደግ ወሳኝ የቤት ሥራ ሆኗል። "በዶላር ላይ ጥገኝነት አይኖርም... ቴክኖሎጂው ክፍያዎች በቀላሉ እንዲተላለፉ ያስችላል። ነገር ግን ወደ ተግባራዊ ትግበራው ስንመጣ፣ የሕግ ማዕቀፍ ጣልቃ ገብነት ያስፈልገዋል። በህግ በኩል፣ ሁለቱ ሀገራት ክፍያው እንዴት እንደሚፈጸምና የገንዘብ ምንዛሪው እንዴት እንደሚሆን መስማማት አለባቸው።" ሲሉ የኢት-ስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ዝግጅታችን፣ 'ኢትዮ-ፔይ' ስለሚፈጥረው ዕድል ከኢት-ስዊች ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ጋር እንወያያለን። ቀጥለን የአፍሪካን የኢነርጂ እንቅፋቶችን ከ'ሰስተነብል ኢነርጂ ፎር ኦል' የኢነርጂ ብቃት ባለሙያ ኤልዛቤት ዋንጌሲ ቼጌ እና ከደቡብ አፍሪካ የኤሌክትሪክ እና ኢነርጂ ምክትል ሚኒስትር ሳማንታ ግራሃም-ማሬ ጋር እንፈትሻለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  5. JAN 13

    ፋይዳ በለውጥ መንገድ፡ ዲጂታል ማንነት፣ የመረጃ ሉዓላዊነት እና የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ "ፋይዳ" ከሙከራ ደረጃ አልፎ አሁን ላይ መላውን ሀገራዊ ሥርዓት እያስተሳሰረ ይገኛል። ባንኮችና የክፍያ ሥርዓቶች ከፋይዳ ጋር መገናኘታቸው የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ ትልቅ ዕድል ቢሆንም፣ የዜጎች የግል መረጃ ደኅንነት ለመጠበቅ የተለያዩ ስልቶች እየተተገበሩበት ነው ። "የግል መረጃችሁ በትላልቅ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያዎች እጅ ሆኖ በየትኛው የሕግ ሥልጣን ሥር እንደሚገኝ እንኳን ማወቅ[አይቻልም]፤ ምክንያቱም ይህ የኩባንያዎች ምስጢር ነው። ፋይዳን በሚመለከት ግን አንድ ያደረግነው መልካም ነገር የመረጃ ቅነሳ ወይም 'ዳታ ሚኒማይዜሽን' የተሰኘውን መርህ መከተል ነው ፤ ስለዚህ ስለ አንድ ሰው ብዙ መረጃዎችን አንወስድም።" ሲሉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ ዘሚካኤል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ ፋይዳ እንዴት የዲጂታል ኢኮኖሚው መሠረት እየሆነ ነው? የመረጃ ደኅንነትና ግልጽነትስ እንዴት ይረጋገጣል? የሚሉትን አንጋቢ ጉዳዮች የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዮዳሄ ዘሚካኤል ጋር በጥልቀት እንመረምራለን ።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  6. JAN 2

    ኃይል፣ ወደብ እና ቅርስ፡- የኢትዮጵያ የወደፊት ዕጣ እና የሉዓላዊነት ትግል

    የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባህር ቀጠና በጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ውስጥ ናቸው። እስራኤል ለሶማሌላንድ የሰጠችው ዕውቅና፣ የሁቲ አማጽያን ዛቻ እና ከእስራኤል ጋር የገብበት ፍጥጫ ቀጥሏል፡፡ በሌላ በኩል፣ ከመቅደላ የተዘረፉ ቅርሶቻችንን ከብሪታኒያ ሙዚየም "በብድር" ሳይሆን በክብር የመመለስ ትግል የአፍሪካዊያን ሌላ ሜዳ ሆኗል። "እስራኤል ለሶማሌላንድ ስትራቴጂካዊ ቦታ እና አስፈላጊነት ትኩረት እየሰጠች ነው፤ ምክንያቱም ሁቲዎች በእስራኤል ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ኢላማዎች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት እየሰነዘሩ ነው። ስለዚህ ይህ አንዱ ጉዳይ ነው።" ሲሉ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት መሰናዶ የሶማሌላንድ የሀገርነት እውቅናና ትርጓሜውን ከፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ዳዊት መዝገበ ጋር እንፈትሻለን። ተዘርፈው ለእይታ የሚቀርቡበት የብሪታኒያ ሙዚየም ቅርሶችን "በውሰት" ለአፍሪካ ሀገራት የመስጠት እቅድና የተዘረፉ ቅርሶችን የማስመለስ ሂደት የትግል መልክን በተመለከተም ከቅርስ አስተዳደር እና ጥበቃ ከፍተኛ ተመራማሪ ተስፋዬ አራጌ ጋር እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr
  7. 12/30/2025

    የአፍሪካ የሉዓላዊነት ትግል፡ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ የአስተሳሰብ ነጻነት

    አፍሪካ በአሁኑ ወቅት የዓለም የኃይል ሚዛን በሚቀያየርበት ባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ የራሷን ድምፅ ለማሰማት እና የፖለቲካ ተጽዕኖዋን ለማሳደግ እየጣረች ትገኛለች። "እንደሚታየው አፍሪካ እና እስያ በተለይም ከሩሲያ ጋር ያላቸው ግንኙነት ዘርፈ ብዙ ነው። በትምህርት ረገድም ሰፊ ግንኙነት አለን። እንደ አጋጣሚ ሆኖ አፍሪካ ውስጥ ከሩሲያ ትምህርትን እና ሌሎች ድጋፎችን ለማግኘት የሚያስችሉ የዳታ ማኔጅመንት ዕቅዶች አሉን።" ሲሉ በወሎ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና የፖለቲካ ኢኮኖሚ መምህር ይመር አሊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ አፍሪካ በባለብዙ-ዋልታ ዓለም ውስጥ ያላትን ስልታዊ ቦታ እና ከሩሲያ ጋር ያላትን ተግባራዊ ግንኙነት በወሎ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና የፖለቲካ ኢኮኖሚ መምህር ከሆኑት ይመር አሊ ጋር እንፈትሻለን። በመቀጠልም፣ የአስተሳሰብ ሉዓላዊነትን እና አፍሪካዊ የሆኑ የንድፈ-ሀሳብ እውቀቶችን የማዳበር አስፈላጊነትን የ"ካፒታል ቫዮለንስ " መጽሐፍ ጸሐፊ ዋቪንያ ማካይ ጋር በጥልቀት እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

    1 hr
  8. 12/18/2025

    የኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ምርት አዲስ መልክ

    የኢትዮጵያ የቅመማ ቅመም ዘርፍ ባለው ከፍተኛ እምቅ አቅም ልክ ተገቢውን ዋጋ አላገኘም። በሌላ በኩል ደግሞ አፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማስፈን በደቡብ-ደቡብ ትብብር እና በሩሲያ-አፍሪካ ትብብር ላይ እየሰራች ነው። የጓሮ እርሻዎች ተባባሪ መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቅድስት አምዴ "እኛ ጋር ወደ 23 የሚደርሱ የምግብ ቅመሞች አሉ። ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹን እናውቃቸዋለን፤ አንዳንዶቹን አናውቃቸውም። ወደ 800 የሚጠጉ የመድኃኒት ዕፅዋትም አሉን። ይህ በጣም ሰፊ የልዩ ልዩ ዝርያዎች ሀብት ነው። በየቦታው አይገኝም። ስለዚህ በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቅ ዕድል አለ ብዬ አስባለሁ።" ስትል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግራለች፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የጉዋሮ ማይክሮ-ፋብሪካዎች የአርሶ አደሩን ገቢ እና የሀገርን የግብርና ዘርፍ መዋቅር እንዴት እየቀየሩ ነው? የሚለውን እንመለከታለን። ለዚህም የጓሮ እርሻዎች ተባባሪ መስራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ቅደስት አምዴን ጋብዘናል። እንዲሁም፣ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የግብርና ኮሌጅ ዲን ዘሪሁን ደምረው (ዶ/ር) እና ሌሎች ዓለም አቀፍ ባለሙያዎች አፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነትን በቴክኖሎጂ፣ በፋይናንስና በትብብር እንዴት ታረጋግጣለች? በሚለው ዙሪያ ያደረጉትን ውይይት እንፈትሻለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

    1 hr

About

''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.