Continental Drift

Eden Teshome

''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.

  1. 15h ago

    የኮንፈረንስ ቱሪዝም፡ አፍሪካ ከ3.1 ትሪሊዮን ዶላር ዘርፍ እንዴት ትጠቀም?

    "የዝግጅቶች የጉባኤ ወይም MICE ቱሪዝም በመባል የሚታወቀው ዘርፍ በ180 ሀገራት ውስጥ በተደረጉ የተለያዩ ስብሰባዎች ወደ 1.6 ቢሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን አዘዋውሯል፤ 1.3 ትሪሊዮን ዶላር ገቢም አስገኝቷል። ስለዚህ በቢሊዮኖች ሳይሆን በትሪሊዮኖች የሚቆጠር ነው። ይህም በቀጥታ ሽያጭ ብቻ የሚገኝ ነው። ከእሱ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሌሎች ኢንዱስትሪዎች ሲጨምር ወደ 3.1 ትሪሊዮን ዶላር በላይ የንግድ ሽያጭ ይደርሳል። ይህም በጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ሲሰላ 1.8 ትሪሊዮን ዶላር አካባቢ ነው። በእርግጥ ይህ ኢንዱስትሪ ራሱ በዓለም ላይ ካሉ ትልልቅ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ስለዚህ ከአንድ ሀገር ኢኮኖሚ አንፃር ስንየው፣ በዓለም ላይ ካሉ ትልልቅ ኢኮኖሚዎች 16ኛ ደረጃ ላይ እንደሚያስቀምጠው እገምታለሁ።" ሲሉ ዮአዳን ጥላሁን፣ የ«ፍሎውለስ ኢቨንትስ» መስራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ዝግጅቶችና ኤግዚቢሽን አዘጋጆች ማህበር የቀድሞ ፕሬዚዳንት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡   በዛሬው የ«ኮንቲነንታል ድሪፍት» ዝግጅታችን፣ የዝግጅቶችና ስብሰባዎች ኢንዱስትሪ ለዓለምና ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ያለውን ግዙፍ ፋይዳ፣ እንዲሁም ለንግድ፣ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ያለውን ስትራቴጂያዊ ሚና እንቃኛለን። በሁለተኛው ክፍላችን ደግሞ፣ ከኢኮኖሚ ትስስርና ከአህጉራዊ ትብብር አንፃር የአፍሪካ ወደብ አልባ ሀገራት የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶችና ዕድሎች ከፖሊሲ አማካሪ ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ (ዶ/ር)ጋር እንዳስሳለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበዉን ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

  2. 5d ago

    የኢንሹራንስ ዘርፍ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ጽናት ያለው ወሳኝ ፋይዳ

    በአብዛኛው የኢንሹራንስ አገልግሎት ከጉዳት በኋላ የሚደረግ ማካካሻ ተደርጎ ይታሰባል። ነገር ግን የኢንሹራንስ ዘርፍ ከዚህም በላይ ለኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ምሰሶ በመሆን ኢንቨስትመንትን በመሳብ፣ መሠረተ ልማትን በማስፋፋት እና አገሮች ከድንገተኛ አደጋዎች በፍጥነት እንዲያገግሙ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።"በአፍሪካ ያለው የኢንሹራንስ ዘርፍ አሁን ካለበት የካሳ ክፍያ ብቻ ላይ የሚያተኩር አቀራረብ ወደ የጽናትና የመቋቋም አቅም ኢንቨስትመንት የሚያተኩር ሥርዓት መሸጋገር ይኖርበታል። በዚህ ረገድ የአስተሳሰብ ለውጥ በጣም ያስፈልጋል፤ ምክንያቱም በአሁኑ ወቅት የኢንሹራንስ ተቋማት ይህንን የጥበቃ ክፍተት ለመሙላት አዳዲስ የንግድ ሞዴሎችን እየተገበሩ ነው። ለምሳሌ፣ በአፍሪካ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር በተያያዙ አደጋዎች የሚደርሱ ኪሳራዎች ውስጥ በኢንሹራንስ የሚሸፈነው 0.5 በመቶ ብቻ ነው። በአደጉ ሀገራት ግን ይህ ቁጥር 50 በመቶ ይደርሳል። ስለዚህ ከአየር ንብረት ነክ አደጋዎች አንፃር በአፍሪካ እጅግ ሰፊ የኢንሹራንስ ጥበቃ ክፍተት እንዳለ ይህ በግልጽ ያሳያል።" ፍቅሩ ጸጋዬ በኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ኩባንያ የስትራቴጂና የቢዝነስ ልማት ዋና ኃላፊ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።   በዛሬው የ«ኮንቲነንታል ድሪፍት» ዝግጅታችን፣ ኢንሹራንስ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ጽናት እንዴት ስትራቴጂያዊ ምሰሶ ሊሆን እንደሚችል እንቃኛለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ ፡

  3. 5d ago

    ዘላቂና ፍትሐዊ የልማት መመዘኛዎች ፦ አፍሪካ የኢንዱስትሪ ዕድገቷን እንዴት ታረጋግጥ ?

    በዓለም አቀፍ ደረጃ 'ኢኤስጂ' (አካባቢያዊ፣ ማህበራዊ እና አመራራዊ) ዘላቂ የመልካም ስራ መመዘኛዎች ከተለመደው የማህበራዊ ኃላፊነት ባለፈ የኢንቨስትመንት ፍሰትን፣ የብድር አቅርቦትንና የንግድ ተወዳዳሪነትን የሚወስኑ ወሳኝ መስፈርቶች እየሆኑ መጥተዋል። አፍሪካ የአህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጠናን እውን ለማድረግና የኢንዱስትሪ ልማቷን ለማፋጠን በምትገኝበት በዚህ ወቅት፣ እነዚህ መስፈርቶች ተጨማሪ የፋይናንስና የአቅም ጫና የሚፈጥሩ እንዳይሆኑ ስጋት አለ። "አፍሪካውያን የአካባቢ የበካይ ጋዝ ልቀት ምንጮች ባንሆንም፣ የ'ኢኤስጂ' መመዘኛዎችን ከእኛ አህጉራዊ እና ማህበራዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ጋር አጣጥመን መጠቀም ይኖርብናል። ለአውሮፓ የአካባቢ ልቀትን መቀነስ ዋነኛ አጀንዳ ቢሆንም፣ ለአፍሪካ ግን ዋናው ትኩረት እንደ ሴቶችን ማካተት፣ የፋይናንስ ተጠቃሚነትን ማስፋፋትና የማህበራዊ ክፍተቶችን መሙላት ያሉ ጉዳዮች ላይ መሆን አለበት። እነዚህን መመዘኛዎች ከራሳችን የልማት ቅድመ-አብዮቶች አንፃር ካቀናጀናቸው ሰፊ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እና የካርቦን ገበያን ጨምሮ አዳዲስ የፋይናንስ ምንጮችን ለመክፈት ትልቅ ዕድል ይፈጥርልናል።" ሲሉ ጆሴፍ አዎላቢ — የቀድሞ የዓለም አቀፉ የቻርተርድ ሰርቲፋይድ አካውንታንቶች ማህበር (ACCA) ፕሬዝዳንት እና የካርቦን ገበያና አረንጓዴ ፋይናንስ ዓለም አቀፍ አማካሪ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ እነዚህ ዘላቂ የመልካም ስራ መስፈርቶች ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ዕድገት ማፋጠኛ ሊሆኑ የሚችሉበትንና የአህጉሪቱን የልማት ፍላጎቶች እንዴት ሊደግፉ እንደሚችሉ በሰፊው እንቃኛለን።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

  4. Jul 30

    ከጥሬ ዕቃ ላኪነት ወደ ቀጠናዊ የዋጋ ሰንሰለት፡ አፍሪካ ሀብቷን ውስጣዊ አቅም እንዴት ማቆየት ትችላለች?

    አፍሪካ ለዓለም ገበያ በርካታ ጥሬ ዕቃዎችን የምታቀርብ ቢሆንም፣ ከውጭ ለሚገቡ ምርቶችም ጥገኛ ናት። አሁን ላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ሲመሠረት፣ ትኩረቱ ወደ ቀጠናዊ የዋጋ ሰንሰለቶች ግንባታ እና የሎጂስቲክስ አውታሮችን በማጠናከር ሀብቱ በአህጉሪቱ እንዲቆይ ማድረግ ላይ እየተሸጋገረ ይገኛል። " አብዛኛዎቹ የሎጂስቲክስ ኩባንያዎች ከአፍሪካ አይደሉም፤ ከ90 እስከ 95 በመቶ የሚሆነው የገቢና የወጪ ንግድ ጭነት የሚከናወነው በአውሮፓ ወይም በአሜሪካ ኩባንያዎች ነው። ይህ በወጪያችን ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ በቁጥር ላሳያችሁ፤ ከቻይና ሻንጋይ እስከ ኢትዮጵያ ለአንድ የዕቃ መጫኛ ኮንቴነር የምንከፍለውን ክፍያ እንመልከት..."  ሲሉ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሎጅስቲክስ እና ዕሴት ሰንሰለት ትምህርት ክፍል ኃላፊ መሳይ አየለ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ አፍሪካ የንግድና የሎጂስቲክስ አውታሮቿን በማቀናጀት ከጥሬ ዕቃ ኤክስፖርት ወጥታ የራሷን የዋጋ ሰንሰለት እንዴት መዘርጋት እንዳለባት እንቃኛለን።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

  5. Jul 25

    የሳህል ወጣቶች፣ ፋይናንስ እና ቱሪዝም፡- የአፍሪካ ዕድገት በሂደት ላይ

    አፍሪካ ትልቅ ወጣት ህዝብን ይዛለች፤ ነገር ግን ይህ የዴሞግራፊ ዕድል ወደ እውነተኛ የኢኮኖሚ ውጤት እንዲቀየር የፋይናንስ ተደራሽነት እና ተቋማዊ ማሻሻያዎች ወሳኝ ናቸው።  "የውስጥ ሀብታችንን የምንጠቀምበት መንገድ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለንን ጥገኝነት ለመቀነስ ይረዳናል። ማናቸውም ሀገር ያለ ዓለም አቀፍ ተቋማት ድጋፍ ብቻውን ኢኮኖሚውን ማሳደግ ይችላል ማለቴ አይደለም፤ ድጋፋቸው ያስፈልገናል። ነገር ግን ማድረግ ያለብን ጥገኝነታችንን መቀነስ ነው። የውጭ ተቋማትን አስተዋጽኦ ለመቀነስ ማዕድናችንን ማቀነባበር አለብን። ለምሳሌ በማሊ ከወርቅ ብቻ ብዙ ወጣቶችን ስራ ማስያዝ እና ዓላማዎቻችንን ማሳካት እንችላለን።" — ሲሉ ዣን ፑዲዩጎ፣ የቪዥን ፈንድ ማሊ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የመንግስት የወጣቶች ልማት እና ድህነት ቅነሳ አማካሪ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ በሳህል ቀጣና በተለይም የማሊ ወጣቶች የኢኮኖሚ ማካተት እና በኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ መስፋፋት ዙሪያ የሚደረጉ ወሳኝ ውይይቶችን እንቃኛለን። ለዚህም የቪዥን ፈንድ ማሊ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የመንግስት አማካሪ ዣን ፑዲዩጎ እንዲሁም ዮናስ ፍቅሩ፣ የኢትዮጵያ ቱሪስት አስጎብኚዎች ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት ጋር ቆይታ አድርገናል። ሙሉ መረጃዉን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ፡

  6. Jul 18

    የክህሎት ሉዓላዊነት፡ አፍሪካ በወጣቶቿ ችሎታ የምትገነባው መጻኢ ዕድል

    አፍሪካ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆነው የአህጉሪቱ ህዝብ ከ25 ዓመት በታች ነው። ይህ ግዙፍ የሰው ኃይል ወደ ኢኮኖሚያዊ ውጤት እንዲቀየር፣ ትምህርት እና ሥልጠና ከኢንዱስትሪ ፍላጎት ጋር መጣጣም አለባቸው።  "ኢትዮጵያ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናት። ከ70 በመቶ በላይ የሆነው ህዝባችን ከ30 ዓመት በታች ነው። መንግስት ለስራ ዕድል ፈጠራ ትልቅ ኢላማ በማስቀመጥ ያለውን ቁርጠኝነት አሳይቷል። ይህንን ለማሳካትም በ2020 መጀመሪያ ላይ የተቋቋመውና በአሁኑ ወቅት ወጣት ከሚባሉ ተቋማት አንዱ የሆነው 'የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር' ትልቅ ሚና እየተጫወተ ነው።" ሲሉ በኢትዮጵያ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ብሔራዊ አስተባባሪ እና የ ‘አሶሴሽን ኦፍ ቻርተርድ ሰርቲፋይድ አካውንታንትስ’ (ACCA) ባልደረባ ቃልኪዳን ታደሰ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ አፍሪካ የራሷን የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ለማፍራት የምታደርገውን ጥረት እና ስለ "ክህሎት ሉዓላዊነት" እንወያያለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ ፡

  7. Jun 22

    የህዳሴው ግድብ በቡድን 7 አባል አገራት ስብሰባ፡- የትራምፕ ቃል እና የኢትዮጵያ ሉዓላዊ መብት

    የኢትዮጵያ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን ወሳኝ ከመሆኑ ባለፈ፣ የሉዓላዊነት እና የቀጣናዊ ዲፕሎማሲ ተምሳሌት ሆኗል። በቅርቡ ደግሞ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቡድን 7 (G7) አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ የግድቡ ግንባታ በግብፅ ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑን በመጥቀስ አሜሪካ በድጋሚ የመደራደር ፍላጎት እንዳላት ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡ "ትራምፕ በኢትዮጵያ እና በግብፅ መካከል ለመደራደር ሞክረው ነበር። በመጨረሻም ኢትዮጵያ ሀብቷን የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን የሚገፍ እና ተቀባይነት የሌለው ስምምነት ተረቅቆ ነበር፤ ይሄ ስምምነት በኋላ በባይደን አስተዳደር እንዲነሳ ተደርጓል። አሁን ደግሞ ለፕሬዝዳንት ሲሲ ይህን ሂደት እንደሚጀምሩ ቃል እየገቡ ነው፤ ምንም የተለየ አዲስ ነገር ይዘው እንደሚመጡ አልጠብቅም።" ሲሉ ፈቃአህመድ ነጋሽ፣ የድንበር ተሻጋሪ የውሃ አስተዳደር እና የሃይድሮ-ፖለቲካ አማካሪ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የህዳሴ ግድብን ዲፕሎማሲያዊ እና ህጋዊ ውስብስብነት እንዲሁም የኢትዮጵያን አዳዲስ የኦዲት ማሻሻያዎች በሁለት አቅጣጫዎች እንፈትሻለን። ለዚህም የድንበር ተሻጋሪ የውሃ አስተዳደር እና የሃይድሮ-ፖለቲካ አማካሪ ፈቃአህመድ ነጋሽ እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የገንዘብ ዘርፍ ሀላፊ ተመስገን ጌታዬ ጋር ቆይታ አድርገናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ ፕሮግራሙን ያዳምጡ፡

  8. Jun 8

    ከዕዳ ወደ ፋይናንስ ሉዓላዊነት፡ የአፍሪካ አዲስ የካፒታል ስትራቴጂ

    ኢትዮጵያ ወደ ዘመናዊ የካፒታል ገበያ ሥርዓት የምታደርገው ሽግግር ከኢኮኖሚ ማሻሻያ ባለፈ፣ የሀገሪቱን የፋይናንስ ተቋማት አቅም እና ቁጥጥር የሚፈትን ትልቅ እርምጃ ነው። ይህ ለውጥ ግልጽነትን፣ ጠንካራ የሂሳብ አያያዝን እና ተወዳዳሪ የሆኑ የሀገር ውስጥ የኢንቨስትመንት ባንኮችን መኖር የግድ ይላል። "ገበያው በተለያዩ መንገዶች ዝግጁ መሆን እንዳለበት እናውቃለን። አንደኛው ነገር ግልጽነት እና ተገቢ የሆነ የፋይናንስ መዝገብ አያያዝ አስፈላጊነት ነው። በዚህ ረገድ እንደ IFRS ያሉ የሂሳብ አያያዝ ሥርዓቶች በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ተግባራዊ መደረጋቸው ትልቅ እርምጃ ነው። ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ከ50 በላይ ባለአክሲዮኖች ያሏቸው አክሲዮን ማኅበራት በባለሥልጣኑ ዘንድ መመዝገብ እንዳለባቸው በግልጽ አመልክቷል።" ሲሉ የአዋሽ ኢንቨስትመንት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አንዱዓለም ኃይሉ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡  በዛሬው የኮንቲነንታል ድሪፍት ዝግጅታችን፣ የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ ዝግጁነት እና የአህጉሪቱን የሉዓላዊ ዕዳ ፈተናዎች በሦስት አቅጣጫዎች እንፈትሻለን። ለዚህም ከአዋሽ ኢንቨስትመንት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አንዱዓለም ኃይሉ(ዶ/ር) ፣ ከኤፍ ኤስ ዲ አፍሪካ የሉዓላዊ ዕዳ አማካሪ ሄንሪ ኪየሬሜ እና ከተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን (UNECA) የፋይናንስ ዘርፍ ኃላፊ ሶንያ ኢሶፕማድዬ ጋር ቆይታ አድርገናል።

About

''Continental Drift' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.' is a program tracking the tectonic changes reshaping Africa and redefining the Global South's role in the world. The show explores how policies, markets, and innovation intersect with everyday lives, offering fact-based insights and authentic African perspectives. Through interviews, explainers, and ground-level reporting, the program connects big shifts to real impact making complex issues clear, relevant, and accessible.