Drum of Changes

Zelalem Demissie

From the heart of ancient kingdoms to the pulse of modern cities, a new rhythm echoes across the continent. Africa is rising — a formidable force shaping the world’s future. For generations, Africa has been the most spoken about, yet the least heard. But today, the call is unmistakable: Africa demands its rightful place at the table of global power. Welcome to 'Drum of Changes' — a program dedicated to the stories that matter to Africa. Here, we explore culture, history, art, politics, the economy, and more, all through the lens of Africa itself. 'Drum of Changes' brings you the voices of transformation resonating across the continent.

  1. 6d ago

    ቻድ ከአይ.ሲ.ሲ ለመውጣት ያሳለፈችው ውሳኔ፡ የምዕራቡ ዓለም መሣሪያ ለሆነው ተቋም የአፍሪካ ምላሽ?

    "የምዕራቡ ዓለም የዓለም አቀፉን የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) የራሱን ፍላጎት ማስፈፀሚያ ያደረገው ይመስላል [...] ቻድ ከ አይ.ሲ.ሲ ለመውጣት ያሳለፈችው ውሳኔም ለቀሪው የአፍሪካ አህጉር ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል 'አፍሪካ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን እና የራሷን የፍትህ መንገድ የመቀየስ ጊዜዋ አሁን ነው' የሚል" ሲሉ የሕግ ባለሞያው መታገስ ዉለታው ለስፑትክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ቀዳሚ ዝግጅታችን ቻድ ከዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ለመውጣት የወሰደችውን ርምጃ መነሻ አድርገን የተቋሙን መዋቅራዊ አድልዎ እና በአፍሪካ የሀገርበቀል የፍትህ ስርዓቶችን የመገንባት ጥረቶችን በጥልቀት እንፈትሻለን። ለዚህም በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር እና የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሞያ መታገስ ዉለታው ጋር ተወያይተናል። በሁለተኛው ጉዳያችን ደግሞ፣ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 29 እስከ 30፣ 2026 በአዲስ አበባ የተካሄደውን ወርልድ ፐብሊክ ፎረም መነሻ አድርገን፤ የግብርና ዘርፉን ወደ 21ኛው ክፍለ ዘመን በማሸጋገር ረገድ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሚና እንቃለን። ይህንን ጉዳይ የበለጠ እንዲያብራሩልን ከሩሲያው "ግራሚዮን ፕላስ" ኩባንያ ተወካይ ፓቬል ኮኖቭ ኒኪታ ጋር ተወያይተናል።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  2. Aug 6

    የኤደን ባሕረ ሰላጤ፡ የባሕር ወንበዴዎች እና የኢትዮጵያ ስትራቴጂክ አስፈላጊነት

    የዓለም አቀፉ የባህር ላይ ጉዞ ድርጅት በሶማሊያ የባህር ዳርቻ እና በኤደን ሰላጤ ላይ የባህር ላይ ወንበዴዎች ጥቃት በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ "አሳሳቢ ነው" ብሏል።“ሩሲያ ትራዲሽናል (ባህላዊ) የኢትዮጵያ አጋር ነች ስንል መንግስታት ቢቀያየሩ እንኳን የማይቀያየር ወዳጅነት ነው ያላቸው ማለት ነው። የአድዋን ጦርነት ብናነሳ እንኳን [ከኢትዮጵያ ጋር የቆመች] ብቸኛዋ የአውሮፓ ሀገር ነች አይደለም? [...] ለአፍሪካውያንም እኮ ከሩሲያ የሚቅድም ወዳጅ የለም [...] ዛሬ ሩሲያ የባለብዙ ዋልታ ዓለም ስረዐት ወሳኝ አካል መሆኗ ወደአንድ ወገን አዘንብሎ የነበረውን የአዓለም ግንኙነት ስረዓት ሚዛን ለማስጠበቅ አስችሏል” ሲሉ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህሩ እንዳለ ንጉሴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። የዛሬው ድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን ኢትዮጵያ ከሩሲያ ጋር ያላትን የጠበቀ ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት መሠረት በማድረግ በኤደን ሰላጤ ላይ የባህር ላይ ውንብድናን ለመከላከል ልትጫወት የምትችለውን ስልታዊ ሚና እንቃኛለን። ለዚህም በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንደለ ንጉሴ እንግዳችን ናቸው። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  3. Aug 3

    ታላቁ አሰላለፍ:- የአፍሪካ መንገድ በአዲሱ የባለብዙ ዋልታ ዘመን

    "ዓለም አቀፉ ደቡብ አሁን ከቡድን 7 በበለጠ የዓለምን ኢኮኖሚ በበላይነት እየተቆጣጠረ ነው [...] አዲስ የገንዘብ ሥርዓት ማለት፡ የዶላር ተፅዕኖን የመቀነስ ሂደትን ያፋጥናል፣ አሜሪካ ዶላር በእጇ በመሆ ምክንያት በሀገራት ላይ የምትጥለው ማዕቀብ ታሪክ ሆኖ እንዲቀር ያደርጋል” ሲሉ የኢኮኖሚ ባለሞያ እና የፖሊሲ አማካሪ ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናገሩ።  በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን የምዕራቡ ዓለም ሀገራት ኢኮኖሚያዊ መሰናክሎችን በግንባር ቀደምትነት እየደረደሩ ባሉበት እና ነባር ባለብዙ ወገን ስምምነቶችን ስጋት ላይ በሚጥሉበት በዚህ ወቅት፣ ጠለቅ ያሉ ሁነቶችን መረዳት ለአፍሪካ ስትራቴጂካዊ የወደፊት ጉዞ የሚኖረውን ወሳኝነት እና ከዚህም አንፃር የታዳጊ ኢኮኖሚ ባለቤቶች የሚኖራቸውን የፖሊሲ አማራጮች በጥልቀት እንመረምራለን። ቆስጠንቲኖስ በርኸተስፋ (ዶ/ር) በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በከፍተኛ የፖሊሲ አማካሪነት ያገለገሉ፣ በአፍሪካ ህብረት የፀረ-ሙስና ቦርድ መሪነት የቆዩ ታዋቂ የኢኮኖሚ ባለሞያ እና የፖሊሲ አማካሪ ሲሆኑ፣ በቅርቡም “ታሪፍስ ኤንድ ‘ኒዉክሌር’ ትሬትስ ኦቭ ኤ ኒዉ ኮልድ ዎር” የተሰኘ አዲስ መጽሐፋቸው ልንባብ አብቅተዋል።   ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  4. Jul 18

    ባለብዙ ዋልታ የዓለም ሥርዓት፦ የሩሲያ አፍሪካ ግንኙነት ለፍትሐዊ የዓለም ስርዓት

    “ባለብዙ ዋልታ የዓለም ስረዓት መፈጠር በተለይም ለአፍሪካ አማራጭ የሌው ጉዳይ ነው [...] ሩሲያም ይህንን ነገር ይዛ መቅረቧ አስፈላጊ ነው [...] ሰርጌ ላቭሮቭ ያንሱት እና ስለአፍሪካ ሁለንተናዊ ነፃነት የሚያወሳው ‘የአፍሪካ ዳግም መነቃቃት’ አፍሪካውያን የምንቀበለው ሲሆን፣ ሩሲያ ፍትሃዊ የዓለም ስረዓት እንዲፈጠር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው” ሲሉ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አስራት ኤርሞሎ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ በቀዳሚነት የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ እ.ኤ.አ. ከሐምሌ 7 እስከ 10 ቀን 2026 በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ያደረጉትን ከፍተኛ ደረጃ ጉብኝቶ መነሻ አድርገን የይፋዊ የሥራ ጉብኝቶቹን ስትራቴጂካዊ አንድምታዎች እንቃኛለን። በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ሐሳባቸዉን የሚያጋሩን በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ቅርስ አስተዳደር መምህር፣ ተማራማሪ ዶ/ር አስራት ኤርሞሎ ናቸው። በተከታዩ ጉዳያችን ደግሞ እ.ኤ.አ. ሐምሌ 15 ቀን 2026 የጀመረዉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር ሂደት በተመለከተ ከብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር) ጋር የተደረገን አጠር ያለ ቆይታ ይዞላችሁ ይቀርባል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

  5. Jul 11

    የአፍሪካና ሩሲያ የጋራ ህልም፤ ወደ ባለብዙ ወገን ዓለምአቀፋዊ ሥርዓት

    የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላፍሮቭ ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ነሐሴ 3 1ቀን 2018 ዓ.ም በአፍሪካ ያደረጉትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት በቡሩንዲ አጠናቅቀዋል፡፡ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ የሰርጌላቭሮቭን ይፋዊ የስራ ብዙ የአፍሪካ አገራት የዩኒፖላር ሥርዓትን ለመግታት ወደ ሩሲያ እንደሚመለከቱ ተናግረዋል።  “በምዕራባውያን የበላይነት የሚመራው የዩኒፖላር (የአንድ ወገን) ሥርዓትና መዋቅራዊ ማስተካከያ ፕሮግራሞች (ስትራክቸራል አድጀስትመንት ፕሮግራምስ) በአፍሪካና በተቀረው ዓለም ሁለንተናዊ ዕድገት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድረዋል” ሲሉ በላይ በየነ በጅማ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ታሪክ መምህር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በጅማ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲ እና የፖለቲካ ታሪክ መምህር በላይ በየነን አነጋግረናል። በዚሁ ዝግጅት ሁለተኛው ክፍል በሶሻሊስት የአውሮጳ ሀገራት ውስጥ ከፍተኛ ትምህርታቸውን የተከታተሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣት ኢትዮጵያውያንን አበርክቷቸውን ለመዳሰስ ከቀድሞ የሶሻሊስት ሀገር ተማሪና የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ሰለሞን አሊ (ዶ/ር) ጋር ሰፊ ዉይይት አድርገናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  6. Jul 11

    የመጨረሻው ምሽግ፦ በአገር በቀል ዘሮችና በምግብ ሉዓላዊነት ላይ የተጋረጠው አደጋ በአፍሪካ

    “በምዕራባውያን አምሳል የተነደፉ የግብርና ምርምር ተቋማት፣ የአገር በቀል የእህል ዘሮቻችን አዋጭነትን ዝቅ አድርጎ የመመልከት ዝንባሌ አለባቸው። ነገር ግን እውነታው ዘሮቻችንን ያጣን ዕለት ማንነታችንን የማጣታችን ጉዳይ ነው። በአሁኑ ወቅት እነዚህ የውጭ ኃይሎችና ግዙፍ ኩባንያዎች ሁሉንም ነገር ተቆጣጥረውታል። በአፍሪካ እስካሁን እጃቸውን ያላስገቡበት ብቸኛው ዘርፍ ቢኖር ምግባችንና የምግብ ስርዓታችን ብቻ ነበር። አሁን አሁን ይሄንኑ የመጨረሻ ምሽጋችንን ለመቆጣጠር በከፍተኛ ፍጥነት እየመጡ ነው” ሲሉ ሚሊዮን በላይ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናገሩ።የዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በሩቅ ባሉ ኃይሎች መካከል የሚቀሰቀሱ ግጭቶች እንደምን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን የዕለት ጉርስ ላይ ስጋት እንደሚሆን እንመረምራለን፤ ይህ ሁኔታም የምግብ ዋስትና በሎም ዋነኛ የብሔራዊ ደህንነት እና ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ የመሆኑንም ነገር ያስቃኘናል። ለዚህም የአፍሪካ የምግብ ሉዓላዊነት ጥምረት ዋና አስተባባሪ የሆኑትን ሚሊዮን በላይ (ዶ/ር) አነጋግረናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  7. Jul 8

    የላቭሮቭ ይፋዊ የስራ ጉብኝት፡ ኢትዮጵያ ፣ ብሪክስ እና ባለብዙ ዋልታው ዓለም

    "ሩሲያ ለኢትዮጵያም ሆነ ለአፍሪካ መልካም ወዳጅ ሆና ለዘመናት ቆይታለች። በተቃራኑው ደግሞ የምእራቡ አለም፣ አፍሪካን በማሳነስ በምእራቡ ላይ ጥገኛ ሆና እንድትቀር እየሰራ ይገኛል [...] ሩሲያ ግን የአፈሪካን ራስን የመቻል ፍላጎት በመሰረታዊነት የተረዳች ሀገር ነች" ሲሉ የሕግ ባለሞያ እና የዓለም ማቀፍ ፖለቲካ ተንታኝ ብሩክ መላኩ ለስፑትኒክ ካፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በቀዳሚነት የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሰርጌ ላቭሮቭን የኢትዮጵያ ጉብኝት አንስተን ሁለንተናዊ አንድምታዎቹን እንቃኛለን። ለዚህም የሕግ ባለሞያ እና የዓለም ማቀፍ ፖለቲካ ተንታኝ ብሩክ መላኩን አነጋግረናል። በሁለተኛው ጉዳያችን  በጆሃንስበርግ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር እና የአፍሪካ ጥናት ማዕከል ዳይሬክተር ሰይፈ ታደለ ኪዳኔ (ዶ/ር) ጋር ቆይታ ያደረግን ሲሆን፣ የቅኝ ግዛት ውርስ የሆነው የ"ሉዓላዊነት" እሳቤ በአፍሪካ ያመጣቸውን መዘዞች እንቃኛለን።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

  8. Jun 15

    የተዘረፉ ቅርሶች፡ የአፍሪካን የታሪክ እውነት ለማስመለስ የሚደረገው ዓለም አቀፍ ትግል

    “[…] ከአፍሪካ በጉልበት የተወሰዱ የተለያዩ ቅርሶች ለአፍሪካውያን ባለቤቶቻቸው ሳይመለሱ በአውሮፓ ሙዚየሞች እንዲቆዩ የሚደረገው ደህንነታቸው በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲጠበቅ ነው የሚለው መከራከሪያ እውነታነት የለውም። ምክንያቱም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በአውሮፓ ውስጥ የሚገኙ ብዙ ሙዚየሞች በጦር መሳሪያውች ተደብድበዋልና። በቅርቡ በፈረንሳዩ ሉቭር ሙዚየም ጭምር በርካታ ስርቆቶች ተፈጽመዋል። ስለዚህ በምዕራቡ አገራት ያሉ ሙዚየሞች በሙሉ አስተማማኝ ናቸው ማለት አይቻልም” ሲሉ የማህበራዊ ጉዳዮች ተመራማሪው አሉላ ፓንከረስት (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። የዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በቀዳሚ ጉዳዩ፣ የአፍሪካን የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ትክክለኛ መኖሪያቸው ለመመለስ የሚደረገውን ታሪካዊ፣ ስልታዊ እና ጥልቅ ስሜት የሚንጸባረቅበትን አፍሪካዊ እንቅስቃሴ ያስቃኘናል። ለዚህም የማህበራዊ ጉዳዮች ተመራማሪውን አሉላ ፓንከረስት (ዶ/ር) አነጋግረናል። እ.ኤ.አ. ሰኔ 12 እና 12 ቀን 2026 በአዲስ አበባ የተካሄደው አንደኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ እና የቴክኖሎጂ ውድድር ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የምንቃኝበት ሁለታኛው ጉዳያችን ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ደግሞ ሐሳባቸዉን ሊያጋሩን ብሩክ ከድር (ዶ/ር)፣ አናንድ አንባላጋን እና ፋራይ ቺዳሩን አነጋግረናል።  ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

About

From the heart of ancient kingdoms to the pulse of modern cities, a new rhythm echoes across the continent. Africa is rising — a formidable force shaping the world’s future. For generations, Africa has been the most spoken about, yet the least heard. But today, the call is unmistakable: Africa demands its rightful place at the table of global power. Welcome to 'Drum of Changes' — a program dedicated to the stories that matter to Africa. Here, we explore culture, history, art, politics, the economy, and more, all through the lens of Africa itself. 'Drum of Changes' brings you the voices of transformation resonating across the continent.