የዓለም ዜና

DW Amharic የመስከረም 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና

የኢትዮጵያ መንግሥት አራት ጄኔራልነትን ጨምሮ ለ66 ከፍተኛ ወታደራዊ የጦር መኮንኖች ማዕረጎች ሰጠ። ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድን ቀጠና “ሰላም ለማጠናከር ባላት ቁርጠኝነት” እንደተበረታቱ በአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ ተናገሩ። እስራኤል በጋዛ በፈጸመቻቸው ጥቃቶች 34 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የጤና ባለሥልጣናት አስታወቁ። የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ከአሜሪካ አቻቸው ዶናልድ ትራምፕ እንደሚገናኙ አስታወቁ። የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የኤች-ዋን ቢ (H-1B) ቪዛ አመልካቾች በዓመት 100,000 ዶላር እንዲከፍሉ የሚያስገድድ ትዕዛዝ አጸደቁ።