The Rising South

ወሰንሰገድ አሰፋ

የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

  1. EPISODE 1

    ብሪክስ:- የዓለም አቀፉን ንግድ እና ኢንቨስትመንት ጨዋታ ቀያሪ

    "የብሪክስ ስኬት በመላው ዓለም የሚገኙ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት ያሻሽላል።" ሲሉ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም ላይ የተገኙት የ ሲቢኢ ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ተናገሩ። ኢትዮጵያ አባል የሆነችበት ይህ ህብረት "በዓለም አቀፍ ንግድ እና ኢንቨስትመንት ላይ ሚዛን የሚፈጥር ነው" ብለው በአጽንኦት ተናግረዋል። "ለአብነት ያህል የብሪክስ ባንክን ብንወስድ በማደግ ላይ ላሉ ገበያዎች እጅግ አስፈላጊ ለሆነው መጠነ-ሰፊ የመሠረተ-ልማት ግንባታ ፋይናንስ የሚያቀርብ ነው።" በማለት አክለዋል። 🎤 በፎረሙ ላይ የተሳተፉት የፋይናንስ ባለሙያው አቶ ጌታቸው ባሻህውረድ, የባንክ አማካሪው አቶ አስራት በትሩ እና የኢቲስዊች ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ይልበስ አዲስ ተጨማሪ ሀሳቦችን ሰጥተዋል:- 📲 የዲጂታል ፋይናንስ አብዮት:- የብሎክቼይን ቴክኖሎጂ የገንዘብ ዝውውርን ፈጣን, አስተማማኝ እና ብቁ አድርጎታል። 🌐 ዓለምአቀፋዊ ተሳትፎ:- የኢትዮጵያን ገበያ ለውጪ ባንኮች መክፈት ውድድር, ካፒታል እና የፈጠራ ክህሎትን ስለሚያመጣ የሀገር ውስጥ ባንኮች ራሳቸውን ማብቃት ይኖርባቸዋል። 🎧 ስለኢትዮጵያ የፋይናንስ ማሻሻያ እንዲሁም ይዟቸው ስለሚመጣቸው ዕድሎች የበለጠ ለማወቅ ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ፖድካስት ሙሉውን ፕሮግራም በመከታተል የለውጡ አካል ይሁኑ።

    30 min
  2. EPISODE 3

    የለዉጥ ጎዳና - የኢትዮጵያ ሽግግር ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች

    የኤሌትሪክ ኃይልን በመጠቀም ከብክለት የጸዳ የትራንስፖርት ማዕከል ለመሆን የሚደረግ ኢትዮጵያዊ ጉዞ! 🎙በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት የትራንስፖርት ባለሙያው አቶ ሞገስ ነጋሽ ኢትዮጵያ ከፖሊሲ እስከ ትግበራ ድረስ በትራንስፖርት ረገድ የያዘችውን ጉዞ ፣ እንዲሁም በኬንያ ስለሚካሄደው አውቶኤክስፖ ከቡርኪናፋሶ እና ናይጀሪያ የተሽከርካሪ ምርት ስኬት ጋር አያይዘው ስለ አፍሪካ አረንጓዴ ጉዞ ሀሳባቸውን አጋርተውናል። 🌍 "በኢትዮጵያ ውስጥ ርካሽ የሰው ኃይል አለ....የፀሐይ ብርሃን፣ መልክዓምድራዊ አቀማመጡን ስትመለከት ኢትዮጵያ የቃጣናውን የኤሌትሪክ ተሽከርካሪ ምርት በበላይነት ለመምራት የሚያስችላት ትልቅ ዕድል አለ።" "ኢትዮጵያ ተሽከርካሪን ከመገጣጠም አልጀመረችም....አሰቀድመን መማር ነበረብን። ሥልጠናውን ጋገኘን በኋላ ግን አሁን ላይ በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎችን እየገጣጠምን ነው። ስለ ኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎችም ሥልጠና ብናገኝ፣ አቅሙም ፣ ልምዱም እንዲሁም የተማረ የሰው ኃይል ስላለን የሚከብደን አይደለም።" በማለት አክለዋል። ኢትዮጵያ ስለተያያዘችው የኃይል ለውጥ የበለጠ ለማወቅ ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ይከታተሉ።🔌🌿

    30 min
  3. EPISODE 4

    ያረጁ ትርክቶችን ልሳን መዝጋት: ደቡባዊ ዓለም መጪውን ጊዜ የሚቀረጽበት ሂደት

    በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት በደቡባዊው ትብብር ድርጅት /Organization of Southern Cooperation/ የቴክኖሎጂ ፈጠራ እና ዲጂታላይዜሽን ማበልጸግ ምክትል ዋና ጸኃፊ የሆኑት ሹመቴ ግዛው /ፒ.ኤች.ዲ/ የዓለም አቀፉ የኃይል ሚዛን ስለሚቀየርበት መንገድ ወሳኝ ነጥቦችን አጋርተዋል። “የደቡባዊው ትብብር ድርጅት በታላቁ ደቡባዊ ዓለም ውስጥ የሚገኙ ሀገራትን እና ማኅበረሰቦችን አቅም ማጎልበት ላይ ያምናል። ለአብነት ያህል ባህላዊ እና ሀገር-በቀል ዕውቀቶቻቸውን በመውሰድ ዓለም-አቀፍ በሆኑ መድረኮች ላይ እንዲሰሙ ያደርጋል።" በማለት ተናግረዋል። ምክትል ዋና ሥራ ፈጻሚዉ የዓለም-አቀፉ የፋይናንስ ሥርዓት ሀገራትን ዕዳ ውስጥ የሚዘፍቅ ነው በማለት ተችተዋል። የብሪክስን እሴቶች በሚጋራ መልኩ ባለብዙ ዋልታ እና ባለብዙ ዘርፍ የሆነ አዲስ ሞዴል እንደሚያስፈልግም ጠቁመዋል። የዓለምን ሥርዓት በመቀየር ሂደት ሚዲያ ወሳኝ ሚና ይጫወታል ሲሉ አስረድተዋል ፤ "ስፑትኒክ ሚዲይ እዚህ አፍሪካ-ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሮውን በመክፈቱ እና ፍትህን፣ እኩልነትን፣ ሁሉን አካታችነትን እንዲሁም በራስ ፈጠራ ላይ መሠረትን ያደረገ ትርክት ሳይሆን መሬት ላይ ባለ ተጨባጭ እውነት ላይ ስለሚሠራ ያለኝን አድናቆት መግለጽ እፈልጋለሁ።" በማለት ገልጸዋል። የመጪውን ዓለም ሥርዓት የሚያስቃኘውን ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተላሉ።

    1 hr
  4. EPISODE 5

    የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነት የአፍሪካን የዕዳ ጫና ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬ ይቀይረዋልን?

    የአፍሪካ የዕዳ ጫና ከጠቅላላ የአህጉራዊ ምርት ውስጥ ከ 66 በመቶ በላይ ሆኗል ። ለዚህም ደካማ የብድር ስርዓት እና ሙስና ምክያቶቹ ናቸው፡፡ ይህ የጤና ስርዓት ላይ እና ትምህርትን በማደናቀፍ ረገድም አሉታዊ ሚናን እየተጫወተ ነው። በዛሬው የራይዚንግ ሳዉዝ ዝግጅታችን ከኢትዮጵያ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት የጋበዝናቸዉ ዶ/ር ጀማል መሐመድ እንዲህ ሲሉ ያብራራሉ። “ብድር በግድ ውሰዱ ብለው አያስወስዱንም፡፡ [...] ከጀርባ ግን ብድር እንድንጠይቅ የሚገፋፉ ነግሮች አሉ ፡፡ ወርልድ ባንክም አይ ኤም ኤፍም፡፡ [...] በተለይ አፍሪካ አካባቢ ደግሞ ይህንን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ተቋማት ስለሌሉ አብዛኛው [ብድር] በካፒታል ፍላይት [ብድሩ በሃገር ስም ቢመጣም] ብሩ ተመልሶ ወደ አዉሮፓ እና አሜሪካ ይሄዳል፡፡ በተመሳሳይ [ዕዳዉን ] እኛ እንከፍላለን ፣ አበዳሪዎች ያተርፋሉ" ብለዋል፡፡ የምስራቃዊ ቡድን አቀራረቦችን በተመለከተም ዶ/ር ጀማል መሐመድ:- "የሩሲያ እና የቻይና አቀራረብ በምጣኔ ሃብታዊ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በተለይ የሩሲያ አቀራረብ ከዚያ በላይም ሊሄድ ይችላል፡፡ ምክንያቱም ከነጻነት ትግል ወቅት ጀምሮ ሀገራት ነጻ እንዲሆኑ ሃቀኛ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩት ሩሲያዎች ናቸው፡፡ እስካሁን ያላቸው እሴት ይመስለኛል፡፡ [...] ሌሎቹም አገራት የእነሱን ዓርዓያነት ተክትለው ነበር፡፡ ለአብነት ኩባን መጥቀስ ትችላለህ፡፡ እነ ፊደል ካስትሮ ለኢትዮጵያ እና አንጎላ ድጋፍ ያደረጉት [ለዚያ ነው]” ሲሉ ተናግረዋል። ዶ/ር ጀማል እንደ መፍትሄ ባሉት ሀሳብ:- "አፍሪካውያን እንደመሆናችን መጠን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና በማጠናከር የውጭ ኃይሎች ላይ ጥገኝነትን መቀነስ አለብን። 54 የተለያዩ ኢኮኖሚዎች ያሏት አፍሪካ ታሪፎችን እና የገበያ እንቅፋቶችን በማስወገድ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎችን የሚስብ አንድ ወጥ ገበያ መፍጠር ትችላለች" ብለዋል፡፡ ስለ አፍሪካ የእዳ ጫና እና ከእዳ መውጫ መንገዶች ለማወወቅ ይህንን የ ራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት ይከታተላሉ።

    1 hr
  5. EPISODE 6

    የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ:- የአዋጁ ይዘት እና ቅጣቶቹ

    በኢትዮጵያ የከተሞች መስፋፋት እና እድገት፣ ከሕዝብ ቁጥር እድገትና ለዉጥ ጋር ተዳምሮ በደረቅ ቆሻሻ አወጋገድ ላይ የራሱን የሆነ አሉታዊ ጫና እየፈጠረ ነው፡፡ ይህንንም ተከትሎ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም  ግንቦት 26 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ በዋለው የ33ኛ መደበኛ ስብሰባው ላይ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 1383/2017 ን በሙሉ ደምጽ አፅድቋል። በዚህኛው የራይዚንግ ሳውዝ ቆይታችን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃ፣ መስኖ፣ ቆላማ አካባቢና አካባቢ ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር አወቀ አምዛዬ በጉዳዩ ላይ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡ 🔇ዶ/ር አወቀ ስለዚህኛው አዋጅ ሲያብራሩ:- “ባለፉት ጊዜያት የወጡ ወጥቶ የነበረው አዋጅ ያስከተለው ችግርና ምንም መተግበር ስላልተቻለ፣ ሀገሪቱ እየተበከለች ስለሆነ ቀስ በቀስ ሺፍት እንዲያደርግ ነው። ሁለተኛ ዛሬውኑ ይታገድ ብሎ አይደለም በነገራችን ላይ የወጣው አዋጅ። ስድስት ወር የሽግግር ጊዜ አለ ገና። በስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ከባለ ኢንዱስትሪዎች ጋራ ምክክሮች ይደረጋሉ፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡ 💸አዋጁ ቅጣትን አስመልክቶ ያስቀመጠውን ሲገልጹ፡- “ባለሱቁና አምራቹ ይቀጣል በነገራችን ላይ፤ ሁለት ሺህ ብርና ሶስት ሺህ ብር ለግለሰብ ነው። አምራቾች የእነርሱ ቅጣት ከ50 ሺህ ብር በላይ ነው። እስከ ሁለት መቶ ሺህ ብር የሚደርስ ነው።” በማለት ዶ/ር አወቀ አክለው ተናግረዋል፡፡'' ስለ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ረቂቅ አዋጅ ይዘት እና አዋጁን መተላለፍ ስለሚያስከትላቸው ቅጣቶች የበለጠ ለማወቅ ይህንን የራይዚንግ ሳውዝ ፕሮግራም ይከታተሉ፡፡

    30 min

About

የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።