Turning Africa Forward

በርናባስ ተስፋዬ

Turning Africa Forward - ከቴክኖሎጂ እና አስተዳደር እስከ ባህል፣ ዲፕሎማሲ እና ከዚያም ባለፈ፤ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ ላቀ ደረጃ ለማደግ የምታደርገውን ጽኑ ጉዞ የሚመሩ ምልከታዎችን በዝርዝር እንዳስሳለን።

Episodes

  1. Jun 17

    የ2026 የዓለም ዋንጫ ፡ የቲኬት ዋጋ መናር እና ጂኦፖለቲካ የጋረዱት ተወዳጁ ስፖርት

    ''አሁን ላይ እንደ ስፖርት ባለሙያ መነጋገር ያለብን 'የትኛው ተጫዋች በዚህ አለም ዋንጫ ላይ ሊጎላ ይችላል? ሊዮኔል ሜሲ ምናልባትም በደመቀ ሁኔታ እግር ኳስን እንዴት ይሰናበታል? በሚሉ ውብ ስፖርታዊ እሳቤዎች ላይ ነበረ ። ነገር ግን አሁን ላይ መገናኛ ብዙሃኑን የሞላው የትኬቶችና የአኮሞዴሽን ዋጋ መወደድ እና ከሜዳ ውጪ ያሉ የንግድና የጂኦፖለቲካ ጉዳዮች ናቸው ። ይህ ዳይናሚክ ፕራይሲንግ (እየተለዋወጠ የሚንር የዋጋ ተመን) የትኬት ክፍያ ሁኔታ ውድድሩን ለተርታው ደጋፊ እጅግ አስቸጋሪ አድርጎታል'' ሲል የስፖርት ጋዜጠኛው እስከአድማስ ሙላቱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግሯል። በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስታችን፤ የመጀመሪያው ጉዳይ የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ለአፍሪካ ተጨማሪ የተሳትፎ ቦታዎችን በመስጠት ትልቅ ዕድል ይዞ መጥቷል ቢባልም፣ ደጋፊዎቿ ግን በኢኮኖሚ ጫና ወደ እየተገፉ መሆናቸውን በመገንዘብ ይህ ነገር ለአፍሪካውያን ስጦታ ነው ወይስ የንግድ ማጧጧፊያ? ስንል የስፖርት ጋዜጠኛውን እስከአድማስ ሙላቱን በስልክ አነጋግረን በጥልቀት ፈትሽነዋል ።  በመቀጠል ደግሞ ኢትዮጵያ፣ ከከፍተኛ የነዳጅ ወጪና ጥገኝነት ለመላቀቅና በራስ ታዳሽ ኃይል ለመቆም ያወጣችውን አዲስ መመሪያ እንቃኛለን። በሀገሪቱ ያሉ የመኪና መገጣጠሚያ ተቋማት በሙሉ ትኩረታቸውን ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ብቻ እንዲያዘነብሉ ስለሚያደርገው ፍኖተ ካርታ፣ ስለ መሰረተ ልማት ዝግጅቶች እና የኢንዱስትሪ ነፃነት ዙሪያ ከትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ከፍተኛ አማካሪ ከአቶ አሰፋ ሐዲስ ጋር ፍሬያማ ቆይታ አድርገናል ።  ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  2. Jun 16

    የአቪዬሽን ስትራቴጂካዊ አጋርነት እና የአፍሪካውያን የተቀላጠፈ እንቅስቃሴ

    ''አሁን ላይ የባህረ ሰላጤው አየር መንገዶች ወደ አህጉራችን የሚያደርጉት መስፋፋት ለአፍሪካ አየር መንገዶች ስጋት ሳይሆን፣ አህጉራዊ ትስስራችንን የሚያጠናክር እና ከዓለም አቀፉ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ጋር በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የትብብር ኮሪደር የሚከፍት ትልቅ ዕድል ነው። ዋናው ቁምነገር ብሔራዊ አየር መንገዶቻችን ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን የንግድ አቅምና መዋቅር በማሳደግ፣ የጋራ የአፍሪካ ነፃ የአየር ትራንስፖርት ገበያን በተግባር ለማገዝ ስልታዊ በሆነ መንገድ እንዴት መተባበር እንዳለባቸው ማወቃቸው ላይ ነው'' ሲሉ የአቪዬሽን ዘርፍ ስትራቴጂስት እና አማካሪ ሾን ሜንዲዝ ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስታችን በቀዳሚነት የአቪዬሽን ትስስርን በተመለከተ የኢትሃድ አየር መንገድ ወደ አፍሪካ የሚያደርገው መስፋፋት እና የደቡብ ለደቡብ የንግድ ትስስርን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከአቪዬሽን ዘርፍ ስትራቴጂስት እና አማካሪ ሾን ሜንዲዝ ጋር እንወያያለን። የዲጂታል ጉዞ ፈቃድ (ETA) የአፍሪካውያንን ነፃ እንቅስቃሴ ማቀላጠፍ እና የኢኮኖሚ ህዳሴን ስለማምጣት ከቱሪዝም መዳረሻዎች አማካሪ አንቶኒ ኦቺዬንግ ጋር በጥልቀት እንነጋገራለን። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ ፦

    1 hr
  3. Jun 16

    የአፍሪካ የአየር ክልል ነፃነት እና የውሃ ስነ-ምህዳር መዋቅራዊ ሉዓላዊነት

    ''አፍሪካ የአየር ክልሏን፣ የንግድ ፍሰቷን እና የመንገደኞች እንቅስቃሴን በራሷ እጅ በማስገባት መዋቅራዊ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ አለባት'' ሲሉ የአቪዬሽን ተንታኝ ደሪክ ንሴኮ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።   በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት፤ እ.ኤ.አ ከሰኔ 15 አእስከ ሰኔ 19 ፣ 2026 በቶጎ ሌሜ የሚካሄደው የአፍሪካ አየር ትራንስፖርት ኮንቬንሽን እና ኤክስፖ ለአህጉሪቱ የተዋሃደ የአየር ክልል (SAATM) መፈጠር ምን ዓይነት ተግባራዊ ዕድሎችን ይዞ ይመጣል? የአየር ትኬት ዋጋንና ቀረጥን በመቀነስ ረገድስ ምን ሚና አለው? ስንል ከአቪዬሽን ተንታኝ እና የኤር ስፔስ አፍሪካ መስራች ደሪክ ንሴኮ ጋር ሰፊ ቆይታን አድርገናል። በክፍል ሁለት ደግሞ፣ የአፍሪካን የውሃ ሀብትና ስነ-ምህዳር ከኬሚካል ብክለት ለመጠበቅ የምዕራባውያንን የተጽዕኖ ሞዴሎች በመተው፣ የደቡብ-ለደቡብ የቴክኖሎጂ ሽግግርና የምርምር ትብብሮች ለአህጉሪቱ ሉዓላዊነት ስላላቸው ወሳኝ ጠቀሜታ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህዝብ ጤና ቶክሲኮሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶ/ር ሰብለወርቅ መኮንን ሸገን ጋር በጥልቀት ተወያይተናል።   ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን  ሙሉ ፕሮግራሙን ይከታተሉ ፡

    1 hr
  4. Jun 2

    ከእጅ አዙር ቅኝ ግዛት መሣሪያነት እስከ ፍርደ ገምድልነት፦ የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት መዋቅራዊ ቀውስ

    ''የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (ICC) የዳኝነት ሥልጣን ዓለም አቀፋዊ አይደለም፤ ገለልተኛም አይደለም። ጠንካራ ግለሰቦችና የአፍሪካ መሪዎች የምዕራባውያንን ብሔራዊ ጥቅም ሲፈታተኑ የሮም ስምምነትን መዋቅራዊ ቀዳዳዎች በመጠቀም የማሸማቀቅና ገደብ የማበጀት እርምጃ ይወሰድባቸዋል'' ሲሉ የሕግ ምሁርና ተመራማሪ አቶ መታገስ ውለታው ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት፤ በሮም ስምምነት የተመሠረተው ICC በአፍሪካና በግሎባል ሳውዝ ላይ ስላለው ተፅዕኖ በሰፊው ዳስሰናል። የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ በአይሲሲ ላይ የሰነዘሩትን ብርቱ ትችት መነሻ በማድረግ፤ አፍሪካ የምዕራባውያንን የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት ፖለቲካ ለመመከት እንደ ብሪክስ ያሉ አማራጭ ጥምረቶችንና አህጉራዊ የፍትሕ መዋቅሮችን እንዴት መጠቀም እንዳለባት በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር መታገስ ውለታው ጋር በጥልቀት ተወያይተናል። ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ፦

    1 hr
  5. May 21

    የደቡባዊው ዓለም የኃይል ሽግግርና አፍሪካ በባለብዙ ዋልታ ዓለም ውስጥ

    ''አፍሪካ በዚህ መልቲፖላር ወርልድ እንቅስቃሴ ውስጥ የቻይናንና የሩሲያን እጅና ትከሻ ተደግፋ በርታ መስራት መቻል አለባት። ምዕራባውያን ጦርና ታንክ ሳይልኩ በሚዲያቸው፣ በእርዳታቸውና በብድራቸው የእጅ አዙር ቅኝ ግዛትን በሚያራምዱበት በዚህ ዘመን፣ አፍሪካ ራሷን ማጠናከር ይኖርባታል'' ሲሉ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ተንታኝ ሸዋፈረው ሽታሁን ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።   በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት፤ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ይፋዊ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ ነው፣ በሞስኮ እና በቤጂንግ መካከል የሚገነባው የተቀናጀ አጋርነት እንዲሁም አዲስ ባለብዙ ዋልታ ዓለምን ለመፍጠር የሚደረገው ሽግግር ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ሽግግርና ለደቡባዊ ዓለም ሀገራት ምን ዓይነት መዋቅራዊ ዕድሎችንና አማራጮችን ይዞ ይመጣል? ስንል የፖለቲካል ኢኮኖሚ ተንታኝ ሸዋፈረው ሽታሁን ጋር ሰፊ ቆይታን አድርገናል። በክፍል ሁለት ደግሞ አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ውስጥ ያላትን የቋሚ መቀመጫ ውክልና ማጣት ታሪካዊ ዳራን በመፈተሽ፣ ጉዳዩ ለአፍሪካ የሚደረግ ‘ችሮታ’ ሳይሆን ታሪካዊ በደልን የማረም የዕዳ ክፍያ ስለመሆኑ በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህርና የሕግ ባለሙያ ከሆኑት ከአቶ መታገስ ውለታው ጋር በጥልቀት ተወያይተናል።  ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  6. May 21

    የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አድልዖ እና የአፍሪካ መዋቅራዊ ሉዓላዊነት ግስጋሴ

    ''ዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ነጻነቱን በአግባቡ አውጆ ለፍትህ የተቋቋመ ሳይሆን ለምዕራባውያኑ ብቻ የሚያገለግል የምዕራባውያን ተቋም ሆኗል። በመሆኑም ታማኝነቱን ካጣ የፖለቲካ መሣሪያ ጋር አፍሪካውያን አብረው ሊቀጥሉ የሚችሉበት ምንም ምክንያት የለም'' ሲሉ የሕግ ባለሙያው አቶ ዳንኤል ፍቃዱ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።  በዛሬው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት በክፍል 1 ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በኢራን ንጹሃን ተማሪዎች ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ዝምታን መምረጡ የተቋሙን አድሏዊነት እንዴት እንደሚያጋልጥ ከሕግ ባለሙያው ዳንኤል ፍቃዱ ጋር ያደረግነው ቆይታ ይዘናል፡፡ በክፍል 2 የኢትዮጵያ የብሪክስ የአዲሱ ልማት ባንክ አእና መሰል አማራጭች የሚሰጠው ስልታዊ ፋይዳ በተመለከተ በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ረዳት ፕሮፌሰር ያየው ገነት ጋር ተወያይተናል፡፡ በክፍል 3 ኢትዮጵያ የምዕራባውያንን “መርምሮ ማረድ” ሴራ በመስበር፣ የእንስሳት ሀብቷን ለመታደግ “መርምሮ መለየት” የተሰኘውን አዲስ ሀገር በቀል አሰራር ይፋ ማድረጓን በተመለከተ ፤ ከኢትዮጵያ እንስሳት ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ማቲዎስ ላቀው ጋር የተደረገ ልዩ ቆይታእናቀርባለን።  ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr
  7. May 20

    የድል ቀን ትሩፋትና የአፍሪካ ስነ-ልቦናዊ ነጻነት

    "የበርሊን መውደቅ አውሮፓውያን የበላይ እንዳልሆኑና አፍሪካን ለመግዛት እንዳልተፈጠሩ ያስተማረ ታሪካዊ ክስተት ነው" ሲሉ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አስራት ኤርሞሎ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡ በዛሬው ፕሮግራማችን ሁለት ዋና ዋና አህጉራዊ ጉዳዮችን እንቃኛለን፦ በክፍል 1 የናዚ ፋሺዝም መሸነፍ ግንቦት 1 / May 9 እና የሶቪየት ህብረት የከፈለችው መስዋዕትነት የኮሎኒያሊዝምን የሐሰት ትርክት እንዴት እንዳፈረሰው፤ ይህም ለዛሬው የሩሲያ-አፍሪካ የጋራ ሉዓላዊነትና የጸረ ኒዮ-ኮሎኒያሊዝም ንቅናቄ እንዴት መሰረት እንደሆነ በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አስራት ኤርሞሎ ጋር ያደረግነውን ውይይት እናቀርባለን። በክፍል 2 መሠረተ-ልማት ከጥሬ ዕቃ ማጋዣነት ወጥቶ የራሱን ሕዝብ ወደሚያገለግል የውስጥ እሴት ማደጉን፤ እንደ ሊቲየም እና ኮባልት ያሉ ወሳኝ ማዕድናትን በሀገር ውስጥ ምንዛሬዎች በመገበያየት "ዘመናዊነት ማለት ምዕራባዊነት እንዳልሆነ" የዓለም አቀፍ ጉባኤዎችና የንግድ ትስስር ከፍተኛ አማካሪ ጉንተር ባይሰል ጋር የዳሰስነውን ይዘን ቀርበናል። ሙሉውን መረጃ ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ፦

    1 hr
  8. May 7

    የዓለም አቀፉ የፍትህ ሥርዓት መዛባትና የአፍሪካ ዲጂታል ዘርፍ ህልውና

    ''ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) የተቋቋመው በአፍሪካውያንና ምራባውያኑ ‘አፈንጋጭ’ በሚሏቸው ሀገራት ላይ እርምጃ ለመውሰድ ብቻ ነው። ምዕራባውያንን ኢላማ ሲያደርግ ግን ሕጉ በድንገት ይወገዛል። ሲሉ የሕግ ምሁርና ፓን-አፍሪካኒስት ፕ/ር ፒ.ኤል.ኦ ሉሙምባ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በመጀመሪያው የተርኒንግ አፍሪካ ፎርዋርድ ፖድካስት በክፍል አንድ ዓለም አቀፍ ሕጎችና እንደ ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ያሉ ተቋማት ለምዕራባውያን ፍላጎት እንዴት መሣሪያ እየሆኑ እንደሆነ እንዲሁም አፍሪካ ዲጂታል ቅኝ ግዛትን ለመከላከል መውሰድ ስላለባት እርምጃዎች ከታዋቂው የሕግ ምሁርና ፓን-አፍሪካኒስት ፕ/ር ፒ.ኤል.ኦ ሉሙምባ ጋር ሰፋ ያለ ቆይታ አድርገናል። በክፍል ሁለት ደግሞ “የዲጂታል ከለላ፡ የኢትዮጵያ የሳይበር ሉዓላዊነት መንገድ” በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የግል የሳይበር ደህንነት ኩባንያ (ZSecuredTech) መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሆኑት አቶ ፋሪስ ሙባረክ ጋር ተወያይተናል።  ሙሉውን መረጃ ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

    1 hr

About

Turning Africa Forward - ከቴክኖሎጂ እና አስተዳደር እስከ ባህል፣ ዲፕሎማሲ እና ከዚያም ባለፈ፤ አፍሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ ወደ ላቀ ደረጃ ለማደግ የምታደርገውን ጽኑ ጉዞ የሚመሩ ምልከታዎችን በዝርዝር እንዳስሳለን።